Friday, August 23, 2013

"የኛ ሰፈር እብዶች እና ቀልዶች" ከሚባለው የፌስቡክ ገፅ ላይ ሳነብ ያገኘሁት፡፡ እንደሚያዝናና ስለገመትኩ ለናንተም ላካፍላችሁ፡-

ጎረምሳው ልቡን ያሻፈተችውን ቆንጆ ለሚስትነት ለመጠየቅ አባቷ ቤት ይሄዳል::
......
አባት:- ልጄን ለጋብቻ ልትጠይቅ መጥተህ በአጠገቤ ማስቲካ ታኝካለህ ትንሽ እንኳን አታፍርም? ክብረቢስ
ጎረምሳው:-ይቅርታ ጌታዬ ስለጠጣው አፌ እንዳይሸት ብዬ ነው
አባት:-ጭራሽ መጠጥም ትጠጣለህ?
ጎረምሳው:-አዎ ግን አልፎ አልፎ ናይት ክለብ ስሄድ ብቻ ነው ምጠጣው
አባት:-ናይት ክለብ ስሄድ ብቻ?!! አታፍርም እንዴ ልጄን ለመጠየቅ ስትመጣ?
ጎረምሳው:-ከእስር ቤት ስወጣ ነው መሄድ የጀመርኩት እንጂ በፊት አልሄድም ነበር
አባት:-የባሰ አታምጣ!!!አንተ ሌባ ልጄን ሰርቀህ ልታበላት ነው እንዴ?
ጎረምሳው:-ሌባ አይደለሁም ሰው ገድዬ ነው እስር ቤት የገባሁት
አባት:-ምን!!!! ነብሰ ገዳይ ነህ?
ጎረምሳው:-አይደለሁም የዛን ቀን በጣም ተናድጄ ስለነበር ነው ሰውየው የኛ ጎረቤት ነበር ልጁን ለማግባት ጠይቄው ከለከለኝ ከዛ ገደልኩት::
አባት:-ና እስቲ ልጄ ና እቀፈኝ ለልጄ እንዳንተ አይነት ጥሩ ባል ነበር ስፈልግ የነበረው

ወይ የሰው ነገር

ፍርድቤቱ ጥቅጥቅ ብሎ ሞልቷል፤ ተከሳሹ በሀፍረት አቀርቅሮ ቆሟል፤ ዳኛው ጥቁር ካባቸውን ደርበው ተሰይመዋል፤ ችሎቱ ውስጥ የውጥረት ፀጥታ ሰፍኗል…
ዳኛው ክሱን ማንበብ ጀመሩ
“እንግዲህ የመጀመርያው ክስህ ባለቤትህን በመዶሻ ግንባሯ ላይ ደጋግመህ በመምታት ገለሀታል የሚል ነው…”
በድንገት ከፍርድቤቱ የጀርባ ወንበሮች አካባቢ “ከይሲ! አረመኔ!” የሚል ድምፅ ተሰማ
ዳኛው ክሱን ማንበብ ቀጠሉ
ሁለተኛው ክስ ደሞ የባለቤትህን እናት በመዶሻ በአሰቃቂ ሁኔታ ገለሀል በሚል ነው
አሁንም ከሗላ በኩል “አፈር ብላ! አረመኔ!” የሚል ድምፅ አስተጋባ
ይሄኔ ዳኛው በጣም ተበሳጩና፤ ማነው እንደዚህ ችሎቱን የሚበጠብጠው ፤ እስቲ ወደፊት ተጠጋ! ብለው አስጠሩትና ለምን እነዚህን ነገሮች እንደተናገረ ጠየቁት
ሰውዬውም ዳኛው ፊት ቀርቦ እንዲህ ብሎ መለሰ:-
"አሁን የተከሰሰው ሰውዬ ለ15 አመት ያህል ጎረቤቴ ነበር፤ ባለቤቱን እና አማቹንም አውቃቸዋለሁ ፤ ይሄ ሁሉ አመት ስንኖር ለአንዳንድ ስራዎች ፈልጌ መዶሻ እንዲያውሰኝ ስጠይቀው ሁልጊዜ የለኝም ነበር የሚለኝ … አሁን መዶሻ እያለው እንደከለከለኝ ስለገባኝ ተበሳጭቼ ነው፡፡

Source: www.fb/amanuelhospital

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...