Wednesday, March 19, 2014

ከ‹‹እንጃ›› በስተጀርባ

ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ደመቀ ከበደ የተሰኘ ገጣሚ ያቀረባት ግጥም ስለመሰጠችኝ ላካፍላችሁ ወደድኩ፡፡

==========

እኒያ የኔ ሰዎች

ከወንዝ ወዲያ ማዶ - በሩቅ የማያቸው

‹‹አትመጡም ወይ›› ብዬ - ለምጠይቃቸው

ከአፍ የሚወጣቸው

አንድ ነው ቃላቸው

‹‹እንጃ›› ነው መልሳቸው፤

እኒህም የኔዎች

አጠገቤ ያሉ - ሰርክ የማገኛቸው

ያልገባኝን ጉዳይ - ሁሌ ሳዋያቸው

ምንም ሳይዛነፍ - ‹‹እንጃ›› ነው መልሳቸው፤

‹‹ ከ‹እንጃ› ምሶሶና - ከ‹እንጃ› ባላ፣ ማገር

በ‹እንጃ› ባይ አናፂ - በታነፀች አገር

ከ‹እንጃ› ማለት በቀር

ለጥያቄ ሁሉ - ምላሽም አልነበር?››

ብየ እጠይቃለሁ

ብየ እጨነቃለሁ

ከጥያቄ ጋን ውስጥ - ጥያቄ እጠልቃለሁ፤

የምሬን እኮ ነው፤

‹‹ከ‹እንጃ› ባይ አገሬ

ከ‹እንጃ› የተሻለ - የአገር ምላሽ ባገኝ

‹ለምን?› አስረግዞ - ‹ለምን?› የወለደው - የሚያንገበግበኝ

ምላሽ ያጣሁለት - ጥያቄ ነበረኝ፤››

ብዬ እተክዛለሁ

ከጥያቄዬ ላይ - ጥያቄ እመዛለሁ፤

‹‹ማንን ነው ማዋየው - ወይ የማማክረው

የልቤ ጥያቄ - ልቤን ተረተረው፤››

እያልኩ አስባለሁ - ድንገት እነጉዳለሁ

ከጥያቄዬ ጋር - እወጣ እወርዳለሁ፤

ቢጨንቀኝ ጊዜ እንጂ፤

በ‹‹እንጃ›› አገር ተፈጥሮ - በ‹‹እንጃ›› ምላሽ አድጎ - ‹‹እንጃ›› ሲል ለኖረ

ከ‹‹እንጃ›› ማለት በቀር - ከ‹‹እንጃ›› የተሻለ - መልስም አልነበረ፤

ሀቅ ይኸውላችሁ፤

በዚች አገሬና - በዚች አገራችሁ

‹‹ምን ይበጀን ይሆን›› - ለሚል ጥያቄዬ - ለሚል ጥያቄያችሁ

‹‹እንጃ›› ነው ምላሹ - ‹‹እንጃልህ፣እንጃልሽ›› - ወይም ‹‹እንጃላችሁ››፡፡

© ደመቀ ከበደ

Monday, March 17, 2014

ቴሌ ከማገናኘት ወደ ማቆራረጥ

አማኑኤል ሆስፒታል ከሚባል የፌስቡክ ገፅ ላይ ከታች የተለጠፈውን ምስል ሳየው እኔንም የሚኮረኩረኝ ጉዳይ ስለሆነ ለእናንተም ለማካፈል ወደድኩ፡፡ መቼም ቴሌ ሰው ከሰው ለማቆራረጥ እንጂ ለማገናኘት እየሰራ አይደለም፡፡ እንዲያውም እንደኔ እንደኔ በቴክኖሎጂና መገናኛ ሚኒስቴር ስር ከሚሆን ማቆራረጥ የሚለውን ቃል ለመጠቀም ሲባል ተቋራጭ ድርጅቶች ውስጥ ቢገባ ይሻላል፡፡ ተቋራጭ የሚለው ቃል ኮንትራክተሮችን እንደሚመለከት ባውቅም ሌላ ቃል ላገኝ ስላልቻልኩ ነው፡፡ የቴሌ ኃላፊዎች ሁልጊዜ በተጠየቁ ቁጥር ከ6 ወር በኋላ ይስተካከላል፤ የምትል መልስ አለቻቸው፡፡ ነገር ግን እስካሁን ስንት 6 ወራቶች አለፉ፤ ስራውም አልተሰራም፤ እኛም ከወዳጅ ዘመዶቻችን ጋር መቆራረጣችን ቀጥሏል፤ እስኪ የሚቻል ከሆነ የቤት ስልክ ከነገመዱ ይዞ መዞር መሞከሩ ሳይሻል አይቀርም፡፡

1969212_595442210534076_435274582_n

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...