Friday, December 20, 2013

...
መቼም ቆንጆ ሲታይ ለማድነቅ “ፐ” አይደል የሚባለው?
“ፐ” ብሎ ጀምሮ በ “ፖ” ከሆነ የህይወት ቋጠሮ፣
ለምን ሌላው ከ “ሀ” እስከ “ፈ” ብቻ ቆጥሮ፣
ነፍሱን አይታደግም ለዘንድሮ፡፡
=============
©ካሳሁን ከበደ፤ 2000 ዓ.ም.

Wednesday, December 18, 2013

የማስታወቂያ ባህላችን

ይህ የምታዩት ምስል የምሁሮች መፍለቂያ ከሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ዋናው በር አጠገብ ያነሳሁት ነው፡፡ በትልቁ “ማንኛውንም ማስታወቂያ መለጠፍ ክልክል ነው” የሚል ማስታወቂያ ቢለጠፍም ብዙ ማስታወቂያዎች የሚታዩ ሲሆን፤ ከዚህም ብዙውን ቦታ የሚሸፍኑት በራሱ በዩኒቨርሲቲው የተለጠፉ ናቸው፡፡ በእርግጥ በራሱ አጥር ላይ መለጠፍ መብቱ ቢሆንም፤ አለጣጠፉ ግን በጣም ያስጠላል፡፡ በአግባቡ ቦርድ ነገር ሰቅሎ መለጠፍ ሲቻል፤ በኮላ በማጣበቅ አካባቢ እያቆሸሹ ልክ በየመንገዱ እንደሚለጠፉት ማስታወቂያዎች ነው እየተደረገ ያለው፡፡ በከፍተኛ ትምህርት ተቋም እንደዚህ ሲደረግ አይቶ በየመንገዱ የሚለጥፈው ሰው ታዲያ ለምን ይወቀሳል፡፡Image013

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...