አሁን አሁን የመብራትና የስራ እንዲሁም የመብራትና የሰው ቁርኝት በጣም የሚገርም ነው፡፡ ያለመብራት መስራት ድሮ ቀረ እኮ፡፡ ምክንያቱም ሁሉ ነገር በኮምፒዩተር ነው የሚሰራው፡፡ በተለይማ በመስሪያ ቤቶች አካባቢ የሚስተዋለው መብራት ሲጠፋ የሆነ ብርሃን ያለበት አካባቢ የቢሮው ሰራተኛ ይሰበሰብና መዓት ወሬ ይቸረችራል፡፡ በቤት ጉዳይ፣ በመብራት ጉዳይ፣ ስለሀገሪቷ ተጨባጭ ሁኔታ፣ ስለ ምሳ፣ ወ.ዘ.ተ… ብቻ ምን አለፋችሁ World Atlas ውስጥ የሌለ ነገር ሁሉ ይሰማል፡፡ እናም ምን ልላችሁ ነው፤ የሰው ልጅ ከህያውነቱ ወደ ሮቦትነት ተቀይሯል፤ መብራት ሲጠፋ ልክ እንደ ሮቦት ቀጥ፡፡ ምንም ያክል በእጅ የሚሰራ ስራ ቢኖር እንኳን መብራት ከጠፋ የስራ ሙድ አብሮ ይጠፋል፡፡
This shows the ultimate dependency syndrome of electricity (power). In this world we live in right now, nothing can be done without power and computer. Because it is the time of Artificial Intelligence than natural intelligence.
መብራት ኃይል ደግሞ የሆነ የቁማር ጨዋታ ይጫወት ይመስል ይህን ሁሉ ነገር እያወቀ ጢባ ጢቤ ይጫወታል፡፡ የሚገርመው እኮ የመብራት ኃይል መስሪያ ቤት ራሱ መብራት ከጠፋ ስራ ማቆሙ ነው፡፡ ይህ ሁሉ ተጠራቅሞ የሀገሪቷን ኢኮኖሚ እንደሚያሽመደምደው ሳይታለም የተፈታ፤ ፀሃይ የሞቀው እውነታ ነው፡፡ ባለጉዳይ ይጉላላል፤ ፋብሪካዎች ይቆማሉ፤ የተጀመረ ስራ እንደተጀመረበት ሰዓት ምርታማ ሆነህ መብራት ከመጣ በኋላ መቀጠል አትችልም፡፡
ስለሆነም በእነ ጊቤ፣ ተከዜ፣ አዋሽ፣ እና አባይ አምላክ መብራት ኃይል ወደፊቱን ቢያስተካክል ጥሩ ነው፡፡ “አንድ ጎልና አንድ ባል አያስማምንም” እንደሚባለው መብራት ኃይል እና ቴሌ አንድ ለሀገሪቷ ስለሆኑ አማራጭ መጠቀም አልተቻለም፡፡ ስለዚህም ነው እንደፈለጉ የሚጫወቱብን፡፡ ለማንኛውም ይህ ከላይ የጠቀስኩት ሁሉ እሮሮ መስተካከል አለበት ለማለት ያህል ነው፡፡