Wednesday, February 12, 2014

ሶስት ጉልቻ

መቼም በዚህ ዘመን ተጋቢ በዝቷል፡፡ ያው ሰው ሲጋባ ከሁለት ወደ አንድ እንደሚቀየር ሁሉ ጋብቻን ፈቅደውና ወደው፤ አበድኩልሽ፣ ሞትኩልህ ብለው ጎጆ የሚቀልሱ በበዙበት አገር በአንፃሩ ደግሞ ጋብቻን የሚሸሹ ወንደ-ላጤዎችና ሴተ-ላጤዎች ደግሞ ቤት ይቁጠራቸው እንጂ ቆጥሮ ማን ሊዘልቃቸው፡፡ የሚገርመው አንዳንዶቹ ጋብቻን ከመፍራታቸው የተነሳ እስከ 50 ዓመት እንዲያውም ተገንዘው እስከሚወጡ ድረስ እናትና አባታቸው ቤት ማሙሽና ሚሚ ተብለው የሚኖሩ ብዙ አሉ፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ ተጋብተው፣ ወልደው ከብደው፣ የወርቅ ኢዮቤልዮ የሚያከብሩ በድሮ ዘመን የተባረከ ትዳር የሰጣቸው በጣት የሚቆጠሩ አባትና እናቶች እንዳሉት ሁሉ፤ በዚህ ዘመን ስንመለከት ግን ተጋብተው በማግስቱ ሁላ የፍርድ ቤት ደጃፍ የማይረግጥ ተጋቢ የለም፡፡ ለዚህም ይመስለኛል አንዳንዶቹ ከማግባት ይልቅ አርፈው የእናትና አባታቸው ቤት የሚቀመጡት፡፡ ከሚጋቡት ጥንዶች የበለጠ በየጊዜው የሚፋቱ ጥንዶች በዝተዋል፡፡ በእርግጥ የሚፋቀሩና የሚተሳሰቡ ወጣት ጥንዶች የሉም ማለቴ አይደለም፡፡ ያው በላጤነት የተለመደ ነፃነት እና ትዳር ውስጥ ሊያጋጥሙ የሚችሉትን ነገሮች ቀድሞ አስቦና ተዘጋጅቶ አለመግባት እንዲሁም ከተጋቡ በኋላ የፍቅር መቀነስ ዋና ዋናዎቹ ምክንያቶች እንደሆኑ ይነገራሉ፡፡ ለማንኛውም “ትዳር ጣፋጭ ነው” እንዳለው ደራሲ በእውቀቱ ጣፋጭ ለማድረግ እንጣር፡፡1509313_799126630117386_1591916346_n

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...