መቼም በዚህ ዘመን ተጋቢ በዝቷል፡፡ ያው ሰው ሲጋባ ከሁለት ወደ አንድ እንደሚቀየር ሁሉ ጋብቻን ፈቅደውና ወደው፤ አበድኩልሽ፣ ሞትኩልህ ብለው ጎጆ የሚቀልሱ በበዙበት አገር በአንፃሩ ደግሞ ጋብቻን የሚሸሹ ወንደ-ላጤዎችና ሴተ-ላጤዎች ደግሞ ቤት ይቁጠራቸው እንጂ ቆጥሮ ማን ሊዘልቃቸው፡፡ የሚገርመው አንዳንዶቹ ጋብቻን ከመፍራታቸው የተነሳ እስከ 50 ዓመት እንዲያውም ተገንዘው እስከሚወጡ ድረስ እናትና አባታቸው ቤት ማሙሽና ሚሚ ተብለው የሚኖሩ ብዙ አሉ፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ ተጋብተው፣ ወልደው ከብደው፣ የወርቅ ኢዮቤልዮ የሚያከብሩ በድሮ ዘመን የተባረከ ትዳር የሰጣቸው በጣት የሚቆጠሩ አባትና እናቶች እንዳሉት ሁሉ፤ በዚህ ዘመን ስንመለከት ግን ተጋብተው በማግስቱ ሁላ የፍርድ ቤት ደጃፍ የማይረግጥ ተጋቢ የለም፡፡ ለዚህም ይመስለኛል አንዳንዶቹ ከማግባት ይልቅ አርፈው የእናትና አባታቸው ቤት የሚቀመጡት፡፡ ከሚጋቡት ጥንዶች የበለጠ በየጊዜው የሚፋቱ ጥንዶች በዝተዋል፡፡ በእርግጥ የሚፋቀሩና የሚተሳሰቡ ወጣት ጥንዶች የሉም ማለቴ አይደለም፡፡ ያው በላጤነት የተለመደ ነፃነት እና ትዳር ውስጥ ሊያጋጥሙ የሚችሉትን ነገሮች ቀድሞ አስቦና ተዘጋጅቶ አለመግባት እንዲሁም ከተጋቡ በኋላ የፍቅር መቀነስ ዋና ዋናዎቹ ምክንያቶች እንደሆኑ ይነገራሉ፡፡ ለማንኛውም “ትዳር ጣፋጭ ነው” እንዳለው ደራሲ በእውቀቱ ጣፋጭ ለማድረግ እንጣር፡፡
"ይህ ጦማር ከምንም ዓይነት የፖለቲካ ርዕዮተ-ዓለም ጋር ያልተሳሰረና እንዲሁ በሀገራችን ውስጥ ስለሚከሰቱ አንዳንድ ትዝብቶች ብቻ ሂስ ለማቅረብ የተዘጋጀ ነው፡፡"
Wednesday, February 12, 2014
ሶስት ጉልቻ
Subscribe to:
Posts (Atom)
Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture
Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...

-
የ11ኛው ዙር አጠቃላይ የአዲስ አበባ 20_80 ኮንዶሚኒየም ቤት ፕሮግራም አሸናፊዎች ዝርዝር ለማየት ቀጣዩን ሊንክ ይጫኑ https://drive.google.com/file/d/0B7AnIIjHSJxNVEpqc1V4NXVtMz...
-
ጅቦች መብታችን ማስከበር አለብን በማለት ፍርድ ቤት ቀርበው ክስ መሰረቱ። ጅቦቹም “ቆይ እኛ በዚህች አገር ስንኖር መድሎ ለምን ይፈጸምብናል? ከአንበሳ እኩል እየታየን አይደለም!” በማለት አቤቱታቸውን ለዳኛው ያቀርባሉ፡፡ ...
-
ይህ የምታዩት ምስል የምሁሮች መፍለቂያ ከሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ዋናው በር አጠገብ ያነሳሁት ነው፡፡ በትልቁ “ማንኛውንም ማስታወቂያ መለጠፍ ክልክል ነው” የሚል ማስታወቂያ ቢለጠፍም ብዙ ማስታወቂ...