Tuesday, April 23, 2013

ነጭ ወረቀትና ጥቁር ነጥብ


በጣም የሚዋደዱ ባልና ሚስቶች ነበሩ፡፡ እናም ፍቅራቸውን ለተመለከተ ሰው በጣም ያስቀናሉ፡፡ ይህን ሁሉ ዘመን በሰላምና በፍቅር ሲኖሩ ባልየው ለሚስቱ ታማኝ፣ ቤቱን አጠንክሮ የያዘና በፀባዩ የተመሰገነ ነበር፡፡ ታዲያ ከዕለታት አንድ ቀን ባልዬው ትንሽ ጥፋት ያጠፋና ሚስት ሆዬ ቡራ ከረዩ ትላለች፡፡ የዚህን ጊዜ ባል ምን ሆነሽ ነው፤ እስከዛሬ ያደረኩትን መልካም ነገር ዘንግተሽ እንዴት ዛሬ ይህችን ያልረባች ጥፋት አጋነንሻትብሎ ጠየቀ፡፡ የዚህን ጊዜ ሚስት ምን መሰለህ፤ እስኪ በምሳሌ ልንገርህ፤ አንድ ነጭ ወረቀት ላይ ትንሽ ጥቁር ነጥብ ብትኖር የበለጠ የሚታየው የቱ ይመስልሃልብላ ጥያቄውን በጥያቄ መለሰችለት፡፡ ባልም ጥቁር ነጥቡአለ፡፡ እሷም ይኸውልህ አለችው፤ ከወረቀቱ ይልቅ ትንሿ ነጥብ ጎልታ እንደታዬችህ ሁሉ ከብዙ ጥሩ ስራህ ይልቅ ይህች ትንሿ መጥፎ ስራ ጎልታ ትታያለችአለችው ይባላል፡፡
እናም የወንጀልና የቁርስ ትንሽ የለውም” ብለን እንደምድም፡፡

የስብሰባ አባዜ



ለሁለት ተሰብሳቢዎች ማይክሮፎን መጠቀም ምን የሚሉት ስልጣኔ፤ ምን የሚሉት ቅብጠት ነው ወዳጆቼ፡፡ አንደኛ ለጆሮ ጥሩ አይደለም፡፡ ሁለተኛም የመብራት ፍጆታ ይወስዳል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ በስብሰባ ብዛት የተነሳ አንድ ሁለት ተሰብሳቢዎች ብቻ ቢሆኑም ትልቅ አዳራሽ ውስጥ ገብቶ ሰብሳቢው ድምፁን በማይክሮፎን ደብልቆ ሰበሰበ ለመባል ብቻ የሚደረግ ስር የሌለው ተግባር ነው፡፡ እኔማ አንዳንዴ ሳስበው የኢትዮጵያ ቀሪ ሀብትና ባህል ስብሰባ ብቻ ሆነ እንዴ እላለሁ፡፡ እውነቴን እኮ ነው የምላችሁ ለጥቃቅን ነገር ሁሉ ስብሰባ፤ ስራ ተዘግቶ፤ ደንበኛ እየተጉላላ፡፡ በተለይ በተለይ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ላይ የሚስተዋለው ይኼው ነው፡፡ ደግሞ እኮ ከጥንት ጀምሮ ነው፤ በንጉሱ ጊዜም እንደዚሁ ወሬ ሲያሞቁ ይውሉና የህዝቡን ችግር ይዘነጉት ነበር፤ በደርግ ጊዜም ጓድ ሊቀመንበር በጦር ሜዳም ቢሆን ተናጋሪ በመሆናቸው ብዙ ያወራሉ፤ ይሰበሰባሉ፤ ያሁኑ ይባስ ደግሞ ሁልጊዜ ስብሰባ፡፡ እድገታችን በስብሰባ ብዛት የሚለካ ከሆነ አላውቅም ብቻ፡፡ እኔ እንደሚገባኝ በጋራ ውሳኔ የሚሻ ጠቃሚ ነገር ሲፈጠር ብቻ ነው ስብሰባ የሚያስፈልገው፡፡ 

ስለዚህ መቼም ስብሰባ ይጥፋ ብዬ አልሞግትም፤ ይልቁንም በወግና ባግባብ መሆን አለበት ብዬ ነው የምደመድመው፡፡

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...