Tuesday, April 23, 2013

ነጭ ወረቀትና ጥቁር ነጥብ


በጣም የሚዋደዱ ባልና ሚስቶች ነበሩ፡፡ እናም ፍቅራቸውን ለተመለከተ ሰው በጣም ያስቀናሉ፡፡ ይህን ሁሉ ዘመን በሰላምና በፍቅር ሲኖሩ ባልየው ለሚስቱ ታማኝ፣ ቤቱን አጠንክሮ የያዘና በፀባዩ የተመሰገነ ነበር፡፡ ታዲያ ከዕለታት አንድ ቀን ባልዬው ትንሽ ጥፋት ያጠፋና ሚስት ሆዬ ቡራ ከረዩ ትላለች፡፡ የዚህን ጊዜ ባል ምን ሆነሽ ነው፤ እስከዛሬ ያደረኩትን መልካም ነገር ዘንግተሽ እንዴት ዛሬ ይህችን ያልረባች ጥፋት አጋነንሻትብሎ ጠየቀ፡፡ የዚህን ጊዜ ሚስት ምን መሰለህ፤ እስኪ በምሳሌ ልንገርህ፤ አንድ ነጭ ወረቀት ላይ ትንሽ ጥቁር ነጥብ ብትኖር የበለጠ የሚታየው የቱ ይመስልሃልብላ ጥያቄውን በጥያቄ መለሰችለት፡፡ ባልም ጥቁር ነጥቡአለ፡፡ እሷም ይኸውልህ አለችው፤ ከወረቀቱ ይልቅ ትንሿ ነጥብ ጎልታ እንደታዬችህ ሁሉ ከብዙ ጥሩ ስራህ ይልቅ ይህች ትንሿ መጥፎ ስራ ጎልታ ትታያለችአለችው ይባላል፡፡
እናም የወንጀልና የቁርስ ትንሽ የለውም” ብለን እንደምድም፡፡

No comments:

Post a Comment

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...