ዳና ተከታታይ የቴሌቪዝን ድራማ መተላለፍ ከጀመረ እነሆ 2ኛ ምዕራፍ፤ 24ኛ ክፍል ላይ ደርሷል፡፡ እና በዚህ ክፍል “አይዳ” የተባለችው ገፀ-ባህሪ “እቴቴ” ከተባለችው ጋር በሚያደርጉት የስልክ ቃለ-ምልልስ ላይ “አይዳ” የተቀመጠችበት ፊት ለፊት የሚገኘው ጠረጴዛ ላይ አስተውላችሁ ከሆነ የተዘቀዘቀ የኢትዮጵያ ባንዲራ ወይም ሲዘቀዘቅ የሴኔጋል የሆነ ባንዲራ ይታያል፡፡ ይህ በቀላሉ ታይቶ ችላ የሚባል ነገር አይደለም፡፡ እኔ ትንሽ ስህተት አይቼ ለማጣጣል ሳይሆን፤ ቁጥር ከአንድ ይጀምራል፣ ስህተትም እንዲሁ ከትንሽ ነው የሚጀምረው ብዬ ስለማምን ነው፡፡ ይህ ፕሮግራም በዓለም ዙሪያ የሚተላለፍ እንደመሆኑ መጠን ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ሰዎች የኢትዮጵያ ባንዲራ እንደዛ ሊመስላቸው ይችላል፡፡ ለማንኛውም ከዳይሬክተሩ ጀምሮ እስከ ተራው አርቲስት ድረስ እንደዚህ ዓይነት ነገሮችን በትክክል አስተውለው መስራት አለባቸው ባይ ነኝ፡፡ ይህ የሚመጣው ቸልተኛ ከመሆንና ለስራው ትኩረት ካለመስጠት ይመስለኛል፡፡ ምንም እንኳን በዘርፉ ባለሙያ ባልሆንም ካሜራ የሚይዘውን ቦታ ሁሉ በጥንቃቄ ማስተዋል ያስፈልጋል፡፡ ለዚህም ነው እኮ ኢዲቲንግ ያስፈለገው፡፡ በእርግጥ ተከታታይ ድራማ መስራት አሰልቺ እንደሆነ እሰማለሁ፡፡ ነገር ግን ስራዬ ተብሎ ከተያዘ የሚያቅት ነገር የለም፡፡ ይህን በአጋጣሚ አነሳሁት እንጂ በሚወጡት ፊልሞች ሁሉ አቃቂር ማውጣት ቀላል ነው፡፡ ከካሜራ ጥራት ጀምሮ እስከ ድምፅ ጥራት እንደዚሁም በታሪክ ፍሰታቸው እዚህ ግቡ የማይባሉ ፊልሞች ይወጣሉ እኮ፡፡ ይህን ከማድረግ አራት፣ አምስት ዓመት ፈጅቶ በጥንቃቄ ጥራት ያለውና ሃገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያስጨበጭብና ለኦስካር የሚታጭ ፊልም መስራት አይሻልም ወይ?
"ይህ ጦማር ከምንም ዓይነት የፖለቲካ ርዕዮተ-ዓለም ጋር ያልተሳሰረና እንዲሁ በሀገራችን ውስጥ ስለሚከሰቱ አንዳንድ ትዝብቶች ብቻ ሂስ ለማቅረብ የተዘጋጀ ነው፡፡"
Tuesday, October 29, 2013
Subscribe to:
Posts (Atom)
Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture
Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...

-
የ11ኛው ዙር አጠቃላይ የአዲስ አበባ 20_80 ኮንዶሚኒየም ቤት ፕሮግራም አሸናፊዎች ዝርዝር ለማየት ቀጣዩን ሊንክ ይጫኑ https://drive.google.com/file/d/0B7AnIIjHSJxNVEpqc1V4NXVtMz...
-
ጅቦች መብታችን ማስከበር አለብን በማለት ፍርድ ቤት ቀርበው ክስ መሰረቱ። ጅቦቹም “ቆይ እኛ በዚህች አገር ስንኖር መድሎ ለምን ይፈጸምብናል? ከአንበሳ እኩል እየታየን አይደለም!” በማለት አቤቱታቸውን ለዳኛው ያቀርባሉ፡፡ ...
-
ይህ የምታዩት ምስል የምሁሮች መፍለቂያ ከሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ዋናው በር አጠገብ ያነሳሁት ነው፡፡ በትልቁ “ማንኛውንም ማስታወቂያ መለጠፍ ክልክል ነው” የሚል ማስታወቂያ ቢለጠፍም ብዙ ማስታወቂ...