Tuesday, October 29, 2013

ስለ ዳና ድራማ ክፍል 24

ዳና ተከታታይ የቴሌቪዝን ድራማ መተላለፍ ከጀመረ እነሆ 2ኛ ምዕራፍ፤ 24ኛ ክፍል ላይ ደርሷል፡፡ እና በዚህ ክፍል “አይዳ” የተባለችው ገፀ-ባህሪ “እቴቴ” ከተባለችው ጋር በሚያደርጉት የስልክ ቃለ-ምልልስ ላይ “አይዳ” የተቀመጠችበት ፊት ለፊት የሚገኘው ጠረጴዛ ላይ አስተውላችሁ ከሆነ የተዘቀዘቀ የኢትዮጵያ ባንዲራ ወይም ሲዘቀዘቅ የሴኔጋል የሆነ ባንዲራ ይታያል፡፡ ይህ በቀላሉ ታይቶ ችላ የሚባል ነገር አይደለም፡፡ እኔ ትንሽ ስህተት አይቼ ለማጣጣል ሳይሆን፤ ቁጥር ከአንድ ይጀምራል፣ ስህተትም እንዲሁ ከትንሽ ነው የሚጀምረው ብዬ ስለማምን ነው፡፡ ይህ ፕሮግራም በዓለም ዙሪያ የሚተላለፍ እንደመሆኑ መጠን ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ሰዎች የኢትዮጵያ ባንዲራ እንደዛ ሊመስላቸው ይችላል፡፡ ለማንኛውም ከዳይሬክተሩ ጀምሮ እስከ ተራው አርቲስት ድረስ እንደዚህ ዓይነት ነገሮችን በትክክል አስተውለው መስራት አለባቸው ባይ ነኝ፡፡ ይህ የሚመጣው ቸልተኛ ከመሆንና ለስራው ትኩረት ካለመስጠት ይመስለኛል፡፡ ምንም እንኳን በዘርፉ ባለሙያ ባልሆንም ካሜራ የሚይዘውን ቦታ ሁሉ በጥንቃቄ ማስተዋል ያስፈልጋል፡፡ ለዚህም ነው እኮ ኢዲቲንግ ያስፈለገው፡፡ በእርግጥ ተከታታይ ድራማ መስራት አሰልቺ እንደሆነ እሰማለሁ፡፡ ነገር ግን ስራዬ ተብሎ ከተያዘ የሚያቅት ነገር የለም፡፡ ይህን በአጋጣሚ አነሳሁት እንጂ በሚወጡት ፊልሞች ሁሉ አቃቂር ማውጣት ቀላል ነው፡፡ ከካሜራ ጥራት ጀምሮ እስከ ድምፅ ጥራት እንደዚሁም በታሪክ ፍሰታቸው እዚህ ግቡ የማይባሉ ፊልሞች ይወጣሉ እኮ፡፡ ይህን ከማድረግ አራት፣ አምስት ዓመት ፈጅቶ በጥንቃቄ ጥራት ያለውና ሃገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያስጨበጭብና ለኦስካር የሚታጭ ፊልም መስራት አይሻልም ወይ?

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...