ሚሊኒዬም አዳራሽ የተካሄደ የኮንስትራክሽን እና ፈርኒቸር ኤግዚቢሽን ነበር፡፡ እና ቅዳሜ ዕለት ጓደኛዬ ጋር ወደዛው እናመራለን፡፡ አንድም በትክክል ስለራሱ ድርጅት እና ምርት የሚያስተዋውቅ ሰው ይጠፋል? በየካውንተሩ ሄድን ግን አንዱ ሲፈልገው ዝም ብሎ ይገለፍጣል፤ የሱን ጥርስ ማዬት የናፈቀን ይመስል፡፡ ሌላው ለንቦጩን ጥሎ ፀጥ ብሎ በራሱ የሃሳብ ማዕበል ውስጥ ይጓዛል፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ ኤግዚቢሽን ለሀገሪቷ ለምን ጠቀማት? እኔ መቼም እስከማውቀው ኤግዚቢሽን ላይ እንዲሳተፉ የሚፈቀድላቸው ኩባንያዎች የተሻለ አገልግሎት ወይም ምርት ያላቸውና የገበያ ዕድል እንዲያገኙ የሚያስችል፣ ቀጥታ ከተገልጋዮች ጋር የሚገናኙበት እና ስለ ኩባንያቸውም የሚያስተዋውቁበት ነው፡፡ ይህ ሆኖ እያለ ግን የሚታየው ነገር የተገላበጠ ነው፡፡
"ይህ ጦማር ከምንም ዓይነት የፖለቲካ ርዕዮተ-ዓለም ጋር ያልተሳሰረና እንዲሁ በሀገራችን ውስጥ ስለሚከሰቱ አንዳንድ ትዝብቶች ብቻ ሂስ ለማቅረብ የተዘጋጀ ነው፡፡"
Friday, November 29, 2013
ፉገራ
እኛ ሰፈር ፍቅረኛሞች አሉ እና ሴቷ በጣም ረዥም ሆና በተቃራኒው ደግሞ ወንዱ አጭር ነው፡፡ መቼም ፍቅር እንኳን ቁመት ሌላም ነገር የማይወስነው ጠንካራ ኃይል ያለው ቁርኝት እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ እናም ለምን ተፋቀሩ ብዬ የሞኝ አፌን አልከፍትም፡፡ ግን እንዲሁ ለመቀለድ ያህል የሰፈር ልጆች ምን ቢሉ ጥሩ ነው? “በቁመት ስለማይደራረሱ አብረው ቁመው እንኳን በስልክ ነው የሚነጋገሩት” ብለው ቁጭ፡፡ የኛ ሰው መቼም አቃቂር ለማውጣት የሚችለው የለም፡፡ እነሱ ተመቻችተው ነው እየኖሩ ያሉት፡፡ እኔ ግን ስላሳቀኝ ለናንተም ልንገራችሁ ብዬ ነው የፃፍኩት፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)
Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture
Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...

-
የ11ኛው ዙር አጠቃላይ የአዲስ አበባ 20_80 ኮንዶሚኒየም ቤት ፕሮግራም አሸናፊዎች ዝርዝር ለማየት ቀጣዩን ሊንክ ይጫኑ https://drive.google.com/file/d/0B7AnIIjHSJxNVEpqc1V4NXVtMz...
-
ጅቦች መብታችን ማስከበር አለብን በማለት ፍርድ ቤት ቀርበው ክስ መሰረቱ። ጅቦቹም “ቆይ እኛ በዚህች አገር ስንኖር መድሎ ለምን ይፈጸምብናል? ከአንበሳ እኩል እየታየን አይደለም!” በማለት አቤቱታቸውን ለዳኛው ያቀርባሉ፡፡ ...
-
ይህ የምታዩት ምስል የምሁሮች መፍለቂያ ከሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ዋናው በር አጠገብ ያነሳሁት ነው፡፡ በትልቁ “ማንኛውንም ማስታወቂያ መለጠፍ ክልክል ነው” የሚል ማስታወቂያ ቢለጠፍም ብዙ ማስታወቂ...