Friday, November 29, 2013

ስለ ኤግዚቢሽን…

ሚሊኒዬም አዳራሽ የተካሄደ የኮንስትራክሽን እና ፈርኒቸር ኤግዚቢሽን ነበር፡፡ እና ቅዳሜ ዕለት ጓደኛዬ ጋር ወደዛው እናመራለን፡፡ አንድም በትክክል ስለራሱ ድርጅት እና ምርት የሚያስተዋውቅ ሰው ይጠፋል? በየካውንተሩ ሄድን ግን አንዱ ሲፈልገው ዝም ብሎ ይገለፍጣል፤ የሱን ጥርስ ማዬት የናፈቀን ይመስል፡፡ ሌላው ለንቦጩን ጥሎ ፀጥ ብሎ በራሱ የሃሳብ ማዕበል ውስጥ ይጓዛል፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ ኤግዚቢሽን ለሀገሪቷ ለምን ጠቀማት? እኔ መቼም እስከማውቀው ኤግዚቢሽን ላይ እንዲሳተፉ የሚፈቀድላቸው ኩባንያዎች የተሻለ አገልግሎት ወይም ምርት ያላቸውና የገበያ ዕድል እንዲያገኙ የሚያስችል፣ ቀጥታ ከተገልጋዮች ጋር የሚገናኙበት እና ስለ ኩባንያቸውም የሚያስተዋውቁበት ነው፡፡ ይህ ሆኖ እያለ ግን የሚታየው ነገር የተገላበጠ ነው፡፡

ፉገራ

እኛ ሰፈር ፍቅረኛሞች አሉ እና ሴቷ በጣም ረዥም ሆና በተቃራኒው ደግሞ ወንዱ አጭር ነው፡፡ መቼም ፍቅር እንኳን ቁመት ሌላም ነገር የማይወስነው ጠንካራ ኃይል ያለው ቁርኝት እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ እናም ለምን ተፋቀሩ ብዬ የሞኝ አፌን አልከፍትም፡፡ ግን እንዲሁ ለመቀለድ ያህል የሰፈር ልጆች ምን ቢሉ ጥሩ ነው? “በቁመት ስለማይደራረሱ አብረው ቁመው እንኳን በስልክ ነው የሚነጋገሩት” ብለው ቁጭ፡፡ የኛ ሰው መቼም አቃቂር ለማውጣት የሚችለው የለም፡፡ እነሱ ተመቻችተው ነው እየኖሩ ያሉት፡፡ እኔ ግን ስላሳቀኝ ለናንተም ልንገራችሁ ብዬ ነው የፃፍኩት፡፡

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...