Thursday, April 18, 2013

አንበሳ አውቶባስ


የአዲስ አበባ እድሜ ጠገብ አንበሳ አውቶቡስ ድርጅት በቢሾፍቱ ባስ ከተሰራ ወዲህ የማስታወቂያዎች የደራ ገበያ ማሟሟቂያ ሆኗል፡፡ ክፍያ ይኑረው አይኑረው ባላውቅም ብቻ ድሮ የምናውቀው ቀይ በቢጫ ቀለም አንበሳ አውቶቡስ ዛሬ የኢንዶሚ፣ የአንቦ ውሃ እና ሌሎች ማስታወቂያዎች ጠቅላላ አካሉን ሸፍነውት ስንት ቁጥር እንደሆነ ራሱ ለማወቅ ያዳግታል፡፡ እኔማ ሳስበው እኛ ሀገር ውስጥ ስታንዳርድ እና ብራንድ ስም የሚባል ነገር ለምን አይኖርም እላለሁ፡፡ ላልረባ ጥቅም ከድሮ ጀምሮ ስንጠቀምበት ለምደነው የኖርንበትን ልማድ ቀይረው የማስታወቂያ ድርጅት አስመሰሉት እኮ፡፡

ስለሆነም፤ መንግስት ለሀገሪቷ መልካም ስም በማሰብ የማስታወቂያውን መጠን ራሱ በትንሽ ካሬ ሜትር ለክቶ ቢያደርግ ለራሱም ስታንዳርዱን ጠብቆ ለመቆየት እና ተሳፋሪም ከመደናገር ይድናል፡፡

Monday, April 15, 2013

የድሮና የዘንድሮ ልጅ ባጭሩ


አንድ ጓደኛዬ ያጫወተኝን ልንገራችሁ፡፡ ልጅ እያለን እንደ ስጥ ከቤት ውጪ ተጥለን እናታችን ገበያ ስትሄድ ለጎረቤት አደራ ሰጥታ፤ ምን ብላ?  “እትዬ ጎርፌ ዝናብ ከመጣ የተሰጣውን በርበሬ ስታስገቢ ልጁንም አብረሽ አስገቢው” ተብለን ነው ያደግነው፡፡ ምክንያቱስ ልጅ በሽ ነዋ፤ የዛን ጊዜ፡፡ አሁን ግን የተገላቢጦሽ ሆኗል፡፡ ልጅ ነው እናቱን ለሰው አደራ ሰጥቶ እንደልቡ የሚዞረው፤ ይህም ትዝ ካለችው ነው፡፡

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...