አንዲት ያለአቅሟ ጠጥታ በመጠጥ ድንባዧ የጠፋ ሴት ፖሊስ ጣቢያ ስልክ ትደውልና “የመኪናዬ ዕቃ በሙሉ ተዘርፏልና ድረሱልኝ” ስትል ታመለክታለች፡፡
ተረኛ ፖሊስም የተሰረቀባትን ዕቃ በቅድሚያ እንድታስመዘግብ ሲጠይቃት “መሪው፣ የእጅ ፍሬኑ፣ ማርሹ፣ ፍሪሲዮን፣ የእግር ፍሬንና ነዳጅ መስጫው ሁሉ እንደሌለ” ተናገረችና ስልኩን ዘጋችው፡፡
ከደቂቃዎች በኋላ ሴትየዋ ትንሽ ስካሯ ሲበርድላት ወደ ፖሊስ ጣቢያው መልሳ ትደውልና ለፖሊሱ “ይቅርታ ጌታዬ በስህተት በመኪናዬ የኋላ በር ገብቼ ነው እንጂ ሁሉም ነገር ስላለ በቃ ተውት” ብላቸው እርፍ፡፡
No comments:
Post a Comment