Friday, December 20, 2013

...
መቼም ቆንጆ ሲታይ ለማድነቅ “ፐ” አይደል የሚባለው?
“ፐ” ብሎ ጀምሮ በ “ፖ” ከሆነ የህይወት ቋጠሮ፣
ለምን ሌላው ከ “ሀ” እስከ “ፈ” ብቻ ቆጥሮ፣
ነፍሱን አይታደግም ለዘንድሮ፡፡
=============
©ካሳሁን ከበደ፤ 2000 ዓ.ም.

Wednesday, December 18, 2013

የማስታወቂያ ባህላችን

ይህ የምታዩት ምስል የምሁሮች መፍለቂያ ከሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ዋናው በር አጠገብ ያነሳሁት ነው፡፡ በትልቁ “ማንኛውንም ማስታወቂያ መለጠፍ ክልክል ነው” የሚል ማስታወቂያ ቢለጠፍም ብዙ ማስታወቂያዎች የሚታዩ ሲሆን፤ ከዚህም ብዙውን ቦታ የሚሸፍኑት በራሱ በዩኒቨርሲቲው የተለጠፉ ናቸው፡፡ በእርግጥ በራሱ አጥር ላይ መለጠፍ መብቱ ቢሆንም፤ አለጣጠፉ ግን በጣም ያስጠላል፡፡ በአግባቡ ቦርድ ነገር ሰቅሎ መለጠፍ ሲቻል፤ በኮላ በማጣበቅ አካባቢ እያቆሸሹ ልክ በየመንገዱ እንደሚለጠፉት ማስታወቂያዎች ነው እየተደረገ ያለው፡፡ በከፍተኛ ትምህርት ተቋም እንደዚህ ሲደረግ አይቶ በየመንገዱ የሚለጥፈው ሰው ታዲያ ለምን ይወቀሳል፡፡Image013

Saturday, December 14, 2013

ደደብ ነህ!

ልጅቷ፡ ልትረዳኝ ትችላለህ?

ልጁ፡ በትክክል፤ ምንድን ነው?

ልጅቷ፡ የሆነ ልጅ እንዲወደኝ እፈልጋለሁ

ልጁ፡ ማን ነው?

ልጅቷ፡ ልነግርህ አልችልም

ልጁ፡ እሺ፤ ለምን እንደምትወጂው አትነግሪውም?

ልጅቷ፡ እንዴት ብዬ?

ልጁ፡ በይዋ

ልጅቷ፡ እወድሃለሁ

ልጁ፡ አዎ፤ እንደዛ ማለት ነው

ልጅቷ፡ ደደብ ነህ

Wednesday, December 4, 2013

የሰሞኑ የቦሌ ትዕይንት

በሳውዲ አረቢያ የሚገኙ ህገ-ወጥ የተባሉ እህት ወንድሞቻችን ከሃገር ውጡ ተብለው ወደ እናት ሃገራቸው መመለስ ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ የድሮው አውሮፕላን ማረፊያ ጉምሩክ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ በሰው ብዛት ተጥለቅልቋል፡፡ ለካ ሳውዲ አረቢያን ክልል 15 አድርገናት ነበር፡፡ አይ ይህች እንጀራ፤ ያልፍልናል ብለው ሄደው በግፍ የተባረሩ ወገኖቻችን ናቸው፡፡ በሳውዲ ብዙ ዘመናት ቢያስቆጥሩም የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ወገኖች ሶስት እና አራት ልጆች ወልደው መቀመጣቸው ግን ገርሞኛል፡፡ በጣም ያሳዝናል ህፃናት ልጆች ይዘው የሚመጡት እኮ ብዙ ናቸው፡፡ ፈቃድ ሳይኖራቸው እንዴት ነው ወልደው ልጅ የሚያሰቃዩት? እርግጥ ነው ይህን ያህል ዓመታት ሲቆዩ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው፤ ለምን ተዋለዱ ብዬ አልጠይቅም፡፡ ግን የሰው ሃገር ውስጥ ሲኖር ከኋላ ለሚመጡት ፍጥረቶች ደህንነት ኃላፊነት መውሰድ ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም እዛ የታሰሩበት ቦታ ሁሉ የሚበላ የሚቀመስ ሲያጡ ያማቸዋል፤ ከዛ የከፋም ነገር ሊፈጠር ይችላል፡፡ በእርግጥ ድንገተኛ ዱብ እዳ ስለሆነ ከሆነ በኋላ ነው ችግሩ የተከሰተው፡፡

እኔን ግን ከዚህ የበለጠ ግርም ያለኝ ነገር ባዕዳን አባረዋቸው ሃገር አለን ብለው በገዛ ሃገራቸው እዚሁ የሚያርፉበት ድንኳን አካባቢ ኢትዮጵያውያን ነን የሚሉ ወገኖች ከ30 ብር በማይበልጥ ዋጋ የሚሸጠውን ሲም ካርድ በ60 ብር ሲቸበችቡላቸው ነበር፡፡ እኛ ራስ በራሳችን ካልተዛዘንን የሌላ ሃገር ሰው እንዴት ነው የሚያዝንልን? እናም የድሮው መተሳሰባችን ይቀጥል እላለሁ፡፡

የስብሰባ ትዝብት 2

የሆነ ስብሰባ ተሳትፌ ነበር እና ፅሁፍ አቅራቢው መድረክ ላይ አይኑን ላፕ ቶፕ ላይ ተክሎ በፕሮጀክተሩ ለእኛ እያሳየ ይገኛል፡፡ ካሜራ ማኑ ካሜራውን ብልጭ ሲያደርግ ይደነግጥና ንግግሩን አቋርጦ አይኑን ወደ ካሜራ ማኑ ያዞራል፡፡ ከልማድም ልማድ አለ፤ እንዲህ ዓይነት ልማድ ግን አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ መቼም ከህዝብ ፊት ሆኖ መድረክ መምራትን የመሰለ ታላቅ ጥበብ የለም፡፡ ምክንያቱም የሁሉም ሰው ዓይን እሱ ጋ ነዋ የሚያፈጠው፤ አፍጥጦም አይቀርም የሆነች እንከን ካስተዋለ ሂስ እና አቃቂር ማውጣቱ አይቀርም፡፡ ግን የዚህ ሰውዬ ሁኔታ ከሁሉም የተለየ ነው፤ አንዴ ብቻ አይደለም ፅሁፉ እስከሚያልቅ ድረስ እኮ ነው፡፡ እናም ጠረጠርኩ “ምናልባት ይህ ሰውዬ ጦር ሜዳ ያሳለፈ ይሆን እንዴ? አልያም ደግሞ አንድ ቤተሰቡን በመብረቅ አጥቷል፡፡” እሱማ በህይወት አለ፡፡

Friday, November 29, 2013

ስለ ኤግዚቢሽን…

ሚሊኒዬም አዳራሽ የተካሄደ የኮንስትራክሽን እና ፈርኒቸር ኤግዚቢሽን ነበር፡፡ እና ቅዳሜ ዕለት ጓደኛዬ ጋር ወደዛው እናመራለን፡፡ አንድም በትክክል ስለራሱ ድርጅት እና ምርት የሚያስተዋውቅ ሰው ይጠፋል? በየካውንተሩ ሄድን ግን አንዱ ሲፈልገው ዝም ብሎ ይገለፍጣል፤ የሱን ጥርስ ማዬት የናፈቀን ይመስል፡፡ ሌላው ለንቦጩን ጥሎ ፀጥ ብሎ በራሱ የሃሳብ ማዕበል ውስጥ ይጓዛል፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ ኤግዚቢሽን ለሀገሪቷ ለምን ጠቀማት? እኔ መቼም እስከማውቀው ኤግዚቢሽን ላይ እንዲሳተፉ የሚፈቀድላቸው ኩባንያዎች የተሻለ አገልግሎት ወይም ምርት ያላቸውና የገበያ ዕድል እንዲያገኙ የሚያስችል፣ ቀጥታ ከተገልጋዮች ጋር የሚገናኙበት እና ስለ ኩባንያቸውም የሚያስተዋውቁበት ነው፡፡ ይህ ሆኖ እያለ ግን የሚታየው ነገር የተገላበጠ ነው፡፡

ፉገራ

እኛ ሰፈር ፍቅረኛሞች አሉ እና ሴቷ በጣም ረዥም ሆና በተቃራኒው ደግሞ ወንዱ አጭር ነው፡፡ መቼም ፍቅር እንኳን ቁመት ሌላም ነገር የማይወስነው ጠንካራ ኃይል ያለው ቁርኝት እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ እናም ለምን ተፋቀሩ ብዬ የሞኝ አፌን አልከፍትም፡፡ ግን እንዲሁ ለመቀለድ ያህል የሰፈር ልጆች ምን ቢሉ ጥሩ ነው? “በቁመት ስለማይደራረሱ አብረው ቁመው እንኳን በስልክ ነው የሚነጋገሩት” ብለው ቁጭ፡፡ የኛ ሰው መቼም አቃቂር ለማውጣት የሚችለው የለም፡፡ እነሱ ተመቻችተው ነው እየኖሩ ያሉት፡፡ እኔ ግን ስላሳቀኝ ለናንተም ልንገራችሁ ብዬ ነው የፃፍኩት፡፡

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...