Friday, October 18, 2013

የጨዋታ መልስ ድባብ

የኢትዮጵያ እና የናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ ዕለት ማታ የአልኮል ገበያ ደርቶ ነበር፡፡ ለምን መሰላችሁ፤ መቼም የኛን ሀገር ነገር ከኔ የበለጠ ታውቁታላችሁ፤ ስናሸንፍ ለደስታ ተብሎ መጠጥ ቤት፤ ግብዣ በግብዣ፡፡ ስንሸነፍም እንደዚሁ ለንዴት ማስወገጃ ተብሎ መጠጥ ቤት፡፡ እና የአሁኑ ደግሞ ኢትዮጵያ ትሸነፋለች ብለው ቁማር ያስያዙ አገር ወዳድ ያልሆኑ የናይጄሪያ ደጋፊዎች በደስታ ጮቤ ረግጠው መጠጥ ቤት ያሳልፋሉ፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ኢትዮጵያ በመሸነፏ ቅስማቸው የተሰበረ ንፁህ የኢትዮጵያ ደጋፊዎች እና ኢትዮጵያ ታሸንፋለች ብለው የቆመሩትም ጭምር ንዴቱን ለመርሳት ብለው መጠጥ ቤት ከትመው ነው ያመሹት፡፡ እና በዚህ መሃል የሃገሪቷ የመጠጥ ፍጆታ ከፍ ሳይል አይቀርም ብዬ እጠረጥራለሁ፡፡ የሃገሪቷ GDP በዚህን ያህል ምጣኔ ባያድግም በዕለቱ፡፡ በመሸነፋችን ላዘናችሁ ኢትዮጵያውያን በመልሱ ጨዋታ እናሸንፋለን አይዟችሁ እላለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ትሸነፋለች ብላችሁ ቁማር የበላችሁ ሟርተኞችም ልብ ይስጣችሁ፤ ተመሳሳይ ይሆናል ብላችሁ እንዳትሸወዱ፡፡

No comments:

Post a Comment

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...