የኢትዮጵያ እና የናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ ዕለት ማታ የአልኮል ገበያ ደርቶ ነበር፡፡ ለምን መሰላችሁ፤ መቼም የኛን ሀገር ነገር ከኔ የበለጠ ታውቁታላችሁ፤ ስናሸንፍ ለደስታ ተብሎ መጠጥ ቤት፤ ግብዣ በግብዣ፡፡ ስንሸነፍም እንደዚሁ ለንዴት ማስወገጃ ተብሎ መጠጥ ቤት፡፡ እና የአሁኑ ደግሞ ኢትዮጵያ ትሸነፋለች ብለው ቁማር ያስያዙ አገር ወዳድ ያልሆኑ የናይጄሪያ ደጋፊዎች በደስታ ጮቤ ረግጠው መጠጥ ቤት ያሳልፋሉ፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ኢትዮጵያ በመሸነፏ ቅስማቸው የተሰበረ ንፁህ የኢትዮጵያ ደጋፊዎች እና ኢትዮጵያ ታሸንፋለች ብለው የቆመሩትም ጭምር ንዴቱን ለመርሳት ብለው መጠጥ ቤት ከትመው ነው ያመሹት፡፡ እና በዚህ መሃል የሃገሪቷ የመጠጥ ፍጆታ ከፍ ሳይል አይቀርም ብዬ እጠረጥራለሁ፡፡ የሃገሪቷ GDP በዚህን ያህል ምጣኔ ባያድግም በዕለቱ፡፡ በመሸነፋችን ላዘናችሁ ኢትዮጵያውያን በመልሱ ጨዋታ እናሸንፋለን አይዟችሁ እላለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ትሸነፋለች ብላችሁ ቁማር የበላችሁ ሟርተኞችም ልብ ይስጣችሁ፤ ተመሳሳይ ይሆናል ብላችሁ እንዳትሸወዱ፡፡
No comments:
Post a Comment