"ይህ ጦማር ከምንም ዓይነት የፖለቲካ ርዕዮተ-ዓለም ጋር ያልተሳሰረና እንዲሁ በሀገራችን ውስጥ ስለሚከሰቱ አንዳንድ ትዝብቶች ብቻ ሂስ ለማቅረብ የተዘጋጀ ነው፡፡"
Monday, September 8, 2014
የጳጉሜ ወር ጣጣ
Wednesday, March 19, 2014
ከ‹‹እንጃ›› በስተጀርባ
ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ደመቀ ከበደ የተሰኘ ገጣሚ ያቀረባት ግጥም ስለመሰጠችኝ ላካፍላችሁ ወደድኩ፡፡
==========
እኒያ የኔ ሰዎች
ከወንዝ ወዲያ ማዶ - በሩቅ የማያቸው
‹‹አትመጡም ወይ›› ብዬ - ለምጠይቃቸው
ከአፍ የሚወጣቸው
አንድ ነው ቃላቸው
‹‹እንጃ›› ነው መልሳቸው፤
እኒህም የኔዎች
አጠገቤ ያሉ - ሰርክ የማገኛቸው
ያልገባኝን ጉዳይ - ሁሌ ሳዋያቸው
ምንም ሳይዛነፍ - ‹‹እንጃ›› ነው መልሳቸው፤
‹‹ ከ‹እንጃ› ምሶሶና - ከ‹እንጃ› ባላ፣ ማገር
በ‹እንጃ› ባይ አናፂ - በታነፀች አገር
ከ‹እንጃ› ማለት በቀር
ለጥያቄ ሁሉ - ምላሽም አልነበር?››
ብየ እጠይቃለሁ
ብየ እጨነቃለሁ
ከጥያቄ ጋን ውስጥ - ጥያቄ እጠልቃለሁ፤
የምሬን እኮ ነው፤
‹‹ከ‹እንጃ› ባይ አገሬ
ከ‹እንጃ› የተሻለ - የአገር ምላሽ ባገኝ
‹ለምን?› አስረግዞ - ‹ለምን?› የወለደው - የሚያንገበግበኝ
ምላሽ ያጣሁለት - ጥያቄ ነበረኝ፤››
ብዬ እተክዛለሁ
ከጥያቄዬ ላይ - ጥያቄ እመዛለሁ፤
‹‹ማንን ነው ማዋየው - ወይ የማማክረው
የልቤ ጥያቄ - ልቤን ተረተረው፤››
እያልኩ አስባለሁ - ድንገት እነጉዳለሁ
ከጥያቄዬ ጋር - እወጣ እወርዳለሁ፤
ቢጨንቀኝ ጊዜ እንጂ፤
በ‹‹እንጃ›› አገር ተፈጥሮ - በ‹‹እንጃ›› ምላሽ አድጎ - ‹‹እንጃ›› ሲል ለኖረ
ከ‹‹እንጃ›› ማለት በቀር - ከ‹‹እንጃ›› የተሻለ - መልስም አልነበረ፤
ሀቅ ይኸውላችሁ፤
በዚች አገሬና - በዚች አገራችሁ
‹‹ምን ይበጀን ይሆን›› - ለሚል ጥያቄዬ - ለሚል ጥያቄያችሁ
‹‹እንጃ›› ነው ምላሹ - ‹‹እንጃልህ፣እንጃልሽ›› - ወይም ‹‹እንጃላችሁ››፡፡
© ደመቀ ከበደ
Monday, March 17, 2014
ቴሌ ከማገናኘት ወደ ማቆራረጥ
አማኑኤል ሆስፒታል ከሚባል የፌስቡክ ገፅ ላይ ከታች የተለጠፈውን ምስል ሳየው እኔንም የሚኮረኩረኝ ጉዳይ ስለሆነ ለእናንተም ለማካፈል ወደድኩ፡፡ መቼም ቴሌ ሰው ከሰው ለማቆራረጥ እንጂ ለማገናኘት እየሰራ አይደለም፡፡ እንዲያውም እንደኔ እንደኔ በቴክኖሎጂና መገናኛ ሚኒስቴር ስር ከሚሆን ማቆራረጥ የሚለውን ቃል ለመጠቀም ሲባል ተቋራጭ ድርጅቶች ውስጥ ቢገባ ይሻላል፡፡ ተቋራጭ የሚለው ቃል ኮንትራክተሮችን እንደሚመለከት ባውቅም ሌላ ቃል ላገኝ ስላልቻልኩ ነው፡፡ የቴሌ ኃላፊዎች ሁልጊዜ በተጠየቁ ቁጥር ከ6 ወር በኋላ ይስተካከላል፤ የምትል መልስ አለቻቸው፡፡ ነገር ግን እስካሁን ስንት 6 ወራቶች አለፉ፤ ስራውም አልተሰራም፤ እኛም ከወዳጅ ዘመዶቻችን ጋር መቆራረጣችን ቀጥሏል፤ እስኪ የሚቻል ከሆነ የቤት ስልክ ከነገመዱ ይዞ መዞር መሞከሩ ሳይሻል አይቀርም፡፡
Wednesday, February 12, 2014
ሶስት ጉልቻ
መቼም በዚህ ዘመን ተጋቢ በዝቷል፡፡ ያው ሰው ሲጋባ ከሁለት ወደ አንድ እንደሚቀየር ሁሉ ጋብቻን ፈቅደውና ወደው፤ አበድኩልሽ፣ ሞትኩልህ ብለው ጎጆ የሚቀልሱ በበዙበት አገር በአንፃሩ ደግሞ ጋብቻን የሚሸሹ ወንደ-ላጤዎችና ሴተ-ላጤዎች ደግሞ ቤት ይቁጠራቸው እንጂ ቆጥሮ ማን ሊዘልቃቸው፡፡ የሚገርመው አንዳንዶቹ ጋብቻን ከመፍራታቸው የተነሳ እስከ 50 ዓመት እንዲያውም ተገንዘው እስከሚወጡ ድረስ እናትና አባታቸው ቤት ማሙሽና ሚሚ ተብለው የሚኖሩ ብዙ አሉ፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ ተጋብተው፣ ወልደው ከብደው፣ የወርቅ ኢዮቤልዮ የሚያከብሩ በድሮ ዘመን የተባረከ ትዳር የሰጣቸው በጣት የሚቆጠሩ አባትና እናቶች እንዳሉት ሁሉ፤ በዚህ ዘመን ስንመለከት ግን ተጋብተው በማግስቱ ሁላ የፍርድ ቤት ደጃፍ የማይረግጥ ተጋቢ የለም፡፡ ለዚህም ይመስለኛል አንዳንዶቹ ከማግባት ይልቅ አርፈው የእናትና አባታቸው ቤት የሚቀመጡት፡፡ ከሚጋቡት ጥንዶች የበለጠ በየጊዜው የሚፋቱ ጥንዶች በዝተዋል፡፡ በእርግጥ የሚፋቀሩና የሚተሳሰቡ ወጣት ጥንዶች የሉም ማለቴ አይደለም፡፡ ያው በላጤነት የተለመደ ነፃነት እና ትዳር ውስጥ ሊያጋጥሙ የሚችሉትን ነገሮች ቀድሞ አስቦና ተዘጋጅቶ አለመግባት እንዲሁም ከተጋቡ በኋላ የፍቅር መቀነስ ዋና ዋናዎቹ ምክንያቶች እንደሆኑ ይነገራሉ፡፡ ለማንኛውም “ትዳር ጣፋጭ ነው” እንዳለው ደራሲ በእውቀቱ ጣፋጭ ለማድረግ እንጣር፡፡
Wednesday, January 1, 2014
Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture
Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...

-
የ11ኛው ዙር አጠቃላይ የአዲስ አበባ 20_80 ኮንዶሚኒየም ቤት ፕሮግራም አሸናፊዎች ዝርዝር ለማየት ቀጣዩን ሊንክ ይጫኑ https://drive.google.com/file/d/0B7AnIIjHSJxNVEpqc1V4NXVtMz...
-
ጅቦች መብታችን ማስከበር አለብን በማለት ፍርድ ቤት ቀርበው ክስ መሰረቱ። ጅቦቹም “ቆይ እኛ በዚህች አገር ስንኖር መድሎ ለምን ይፈጸምብናል? ከአንበሳ እኩል እየታየን አይደለም!” በማለት አቤቱታቸውን ለዳኛው ያቀርባሉ፡፡ ...
-
ይህ የምታዩት ምስል የምሁሮች መፍለቂያ ከሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ዋናው በር አጠገብ ያነሳሁት ነው፡፡ በትልቁ “ማንኛውንም ማስታወቂያ መለጠፍ ክልክል ነው” የሚል ማስታወቂያ ቢለጠፍም ብዙ ማስታወቂ...