Tuesday, April 23, 2013

ነጭ ወረቀትና ጥቁር ነጥብ


በጣም የሚዋደዱ ባልና ሚስቶች ነበሩ፡፡ እናም ፍቅራቸውን ለተመለከተ ሰው በጣም ያስቀናሉ፡፡ ይህን ሁሉ ዘመን በሰላምና በፍቅር ሲኖሩ ባልየው ለሚስቱ ታማኝ፣ ቤቱን አጠንክሮ የያዘና በፀባዩ የተመሰገነ ነበር፡፡ ታዲያ ከዕለታት አንድ ቀን ባልዬው ትንሽ ጥፋት ያጠፋና ሚስት ሆዬ ቡራ ከረዩ ትላለች፡፡ የዚህን ጊዜ ባል ምን ሆነሽ ነው፤ እስከዛሬ ያደረኩትን መልካም ነገር ዘንግተሽ እንዴት ዛሬ ይህችን ያልረባች ጥፋት አጋነንሻትብሎ ጠየቀ፡፡ የዚህን ጊዜ ሚስት ምን መሰለህ፤ እስኪ በምሳሌ ልንገርህ፤ አንድ ነጭ ወረቀት ላይ ትንሽ ጥቁር ነጥብ ብትኖር የበለጠ የሚታየው የቱ ይመስልሃልብላ ጥያቄውን በጥያቄ መለሰችለት፡፡ ባልም ጥቁር ነጥቡአለ፡፡ እሷም ይኸውልህ አለችው፤ ከወረቀቱ ይልቅ ትንሿ ነጥብ ጎልታ እንደታዬችህ ሁሉ ከብዙ ጥሩ ስራህ ይልቅ ይህች ትንሿ መጥፎ ስራ ጎልታ ትታያለችአለችው ይባላል፡፡
እናም የወንጀልና የቁርስ ትንሽ የለውም” ብለን እንደምድም፡፡

የስብሰባ አባዜ



ለሁለት ተሰብሳቢዎች ማይክሮፎን መጠቀም ምን የሚሉት ስልጣኔ፤ ምን የሚሉት ቅብጠት ነው ወዳጆቼ፡፡ አንደኛ ለጆሮ ጥሩ አይደለም፡፡ ሁለተኛም የመብራት ፍጆታ ይወስዳል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ በስብሰባ ብዛት የተነሳ አንድ ሁለት ተሰብሳቢዎች ብቻ ቢሆኑም ትልቅ አዳራሽ ውስጥ ገብቶ ሰብሳቢው ድምፁን በማይክሮፎን ደብልቆ ሰበሰበ ለመባል ብቻ የሚደረግ ስር የሌለው ተግባር ነው፡፡ እኔማ አንዳንዴ ሳስበው የኢትዮጵያ ቀሪ ሀብትና ባህል ስብሰባ ብቻ ሆነ እንዴ እላለሁ፡፡ እውነቴን እኮ ነው የምላችሁ ለጥቃቅን ነገር ሁሉ ስብሰባ፤ ስራ ተዘግቶ፤ ደንበኛ እየተጉላላ፡፡ በተለይ በተለይ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ላይ የሚስተዋለው ይኼው ነው፡፡ ደግሞ እኮ ከጥንት ጀምሮ ነው፤ በንጉሱ ጊዜም እንደዚሁ ወሬ ሲያሞቁ ይውሉና የህዝቡን ችግር ይዘነጉት ነበር፤ በደርግ ጊዜም ጓድ ሊቀመንበር በጦር ሜዳም ቢሆን ተናጋሪ በመሆናቸው ብዙ ያወራሉ፤ ይሰበሰባሉ፤ ያሁኑ ይባስ ደግሞ ሁልጊዜ ስብሰባ፡፡ እድገታችን በስብሰባ ብዛት የሚለካ ከሆነ አላውቅም ብቻ፡፡ እኔ እንደሚገባኝ በጋራ ውሳኔ የሚሻ ጠቃሚ ነገር ሲፈጠር ብቻ ነው ስብሰባ የሚያስፈልገው፡፡ 

ስለዚህ መቼም ስብሰባ ይጥፋ ብዬ አልሞግትም፤ ይልቁንም በወግና ባግባብ መሆን አለበት ብዬ ነው የምደመድመው፡፡

Thursday, April 18, 2013

አንበሳ አውቶባስ


የአዲስ አበባ እድሜ ጠገብ አንበሳ አውቶቡስ ድርጅት በቢሾፍቱ ባስ ከተሰራ ወዲህ የማስታወቂያዎች የደራ ገበያ ማሟሟቂያ ሆኗል፡፡ ክፍያ ይኑረው አይኑረው ባላውቅም ብቻ ድሮ የምናውቀው ቀይ በቢጫ ቀለም አንበሳ አውቶቡስ ዛሬ የኢንዶሚ፣ የአንቦ ውሃ እና ሌሎች ማስታወቂያዎች ጠቅላላ አካሉን ሸፍነውት ስንት ቁጥር እንደሆነ ራሱ ለማወቅ ያዳግታል፡፡ እኔማ ሳስበው እኛ ሀገር ውስጥ ስታንዳርድ እና ብራንድ ስም የሚባል ነገር ለምን አይኖርም እላለሁ፡፡ ላልረባ ጥቅም ከድሮ ጀምሮ ስንጠቀምበት ለምደነው የኖርንበትን ልማድ ቀይረው የማስታወቂያ ድርጅት አስመሰሉት እኮ፡፡

ስለሆነም፤ መንግስት ለሀገሪቷ መልካም ስም በማሰብ የማስታወቂያውን መጠን ራሱ በትንሽ ካሬ ሜትር ለክቶ ቢያደርግ ለራሱም ስታንዳርዱን ጠብቆ ለመቆየት እና ተሳፋሪም ከመደናገር ይድናል፡፡

Monday, April 15, 2013

የድሮና የዘንድሮ ልጅ ባጭሩ


አንድ ጓደኛዬ ያጫወተኝን ልንገራችሁ፡፡ ልጅ እያለን እንደ ስጥ ከቤት ውጪ ተጥለን እናታችን ገበያ ስትሄድ ለጎረቤት አደራ ሰጥታ፤ ምን ብላ?  “እትዬ ጎርፌ ዝናብ ከመጣ የተሰጣውን በርበሬ ስታስገቢ ልጁንም አብረሽ አስገቢው” ተብለን ነው ያደግነው፡፡ ምክንያቱስ ልጅ በሽ ነዋ፤ የዛን ጊዜ፡፡ አሁን ግን የተገላቢጦሽ ሆኗል፡፡ ልጅ ነው እናቱን ለሰው አደራ ሰጥቶ እንደልቡ የሚዞረው፤ ይህም ትዝ ካለችው ነው፡፡

Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture

Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...