...
መቼም ቆንጆ ሲታይ ለማድነቅ “ፐ” አይደል የሚባለው?
“ፐ” ብሎ ጀምሮ በ “ፖ” ከሆነ የህይወት ቋጠሮ፣
ለምን ሌላው ከ “ሀ” እስከ “ፈ” ብቻ ቆጥሮ፣
ነፍሱን አይታደግም ለዘንድሮ፡፡
=============
©ካሳሁን ከበደ፤ 2000 ዓ.ም.
"ይህ ጦማር ከምንም ዓይነት የፖለቲካ ርዕዮተ-ዓለም ጋር ያልተሳሰረና እንዲሁ በሀገራችን ውስጥ ስለሚከሰቱ አንዳንድ ትዝብቶች ብቻ ሂስ ለማቅረብ የተዘጋጀ ነው፡፡"
Friday, December 20, 2013
Wednesday, December 18, 2013
የማስታወቂያ ባህላችን
ይህ የምታዩት ምስል የምሁሮች መፍለቂያ ከሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ዋናው በር አጠገብ ያነሳሁት ነው፡፡ በትልቁ “ማንኛውንም ማስታወቂያ መለጠፍ ክልክል ነው” የሚል ማስታወቂያ ቢለጠፍም ብዙ ማስታወቂያዎች የሚታዩ ሲሆን፤ ከዚህም ብዙውን ቦታ የሚሸፍኑት በራሱ በዩኒቨርሲቲው የተለጠፉ ናቸው፡፡ በእርግጥ በራሱ አጥር ላይ መለጠፍ መብቱ ቢሆንም፤ አለጣጠፉ ግን በጣም ያስጠላል፡፡ በአግባቡ ቦርድ ነገር ሰቅሎ መለጠፍ ሲቻል፤ በኮላ በማጣበቅ አካባቢ እያቆሸሹ ልክ በየመንገዱ እንደሚለጠፉት ማስታወቂያዎች ነው እየተደረገ ያለው፡፡ በከፍተኛ ትምህርት ተቋም እንደዚህ ሲደረግ አይቶ በየመንገዱ የሚለጥፈው ሰው ታዲያ ለምን ይወቀሳል፡፡
Saturday, December 14, 2013
ደደብ ነህ!
ልጅቷ፡ ልትረዳኝ ትችላለህ?
ልጁ፡ በትክክል፤ ምንድን ነው?
ልጅቷ፡ የሆነ ልጅ እንዲወደኝ እፈልጋለሁ
ልጁ፡ ማን ነው?
ልጅቷ፡ ልነግርህ አልችልም
ልጁ፡ እሺ፤ ለምን እንደምትወጂው አትነግሪውም?
ልጅቷ፡ እንዴት ብዬ?
ልጁ፡ በይዋ
ልጅቷ፡ እወድሃለሁ
ልጁ፡ አዎ፤ እንደዛ ማለት ነው
ልጅቷ፡ ደደብ ነህ
Wednesday, December 4, 2013
የሰሞኑ የቦሌ ትዕይንት
በሳውዲ አረቢያ የሚገኙ ህገ-ወጥ የተባሉ እህት ወንድሞቻችን ከሃገር ውጡ ተብለው ወደ እናት ሃገራቸው መመለስ ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ የድሮው አውሮፕላን ማረፊያ ጉምሩክ ተብሎ የሚጠራው አካባቢ በሰው ብዛት ተጥለቅልቋል፡፡ ለካ ሳውዲ አረቢያን ክልል 15 አድርገናት ነበር፡፡ አይ ይህች እንጀራ፤ ያልፍልናል ብለው ሄደው በግፍ የተባረሩ ወገኖቻችን ናቸው፡፡ በሳውዲ ብዙ ዘመናት ቢያስቆጥሩም የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ወገኖች ሶስት እና አራት ልጆች ወልደው መቀመጣቸው ግን ገርሞኛል፡፡ በጣም ያሳዝናል ህፃናት ልጆች ይዘው የሚመጡት እኮ ብዙ ናቸው፡፡ ፈቃድ ሳይኖራቸው እንዴት ነው ወልደው ልጅ የሚያሰቃዩት? እርግጥ ነው ይህን ያህል ዓመታት ሲቆዩ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው፤ ለምን ተዋለዱ ብዬ አልጠይቅም፡፡ ግን የሰው ሃገር ውስጥ ሲኖር ከኋላ ለሚመጡት ፍጥረቶች ደህንነት ኃላፊነት መውሰድ ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም እዛ የታሰሩበት ቦታ ሁሉ የሚበላ የሚቀመስ ሲያጡ ያማቸዋል፤ ከዛ የከፋም ነገር ሊፈጠር ይችላል፡፡ በእርግጥ ድንገተኛ ዱብ እዳ ስለሆነ ከሆነ በኋላ ነው ችግሩ የተከሰተው፡፡
እኔን ግን ከዚህ የበለጠ ግርም ያለኝ ነገር ባዕዳን አባረዋቸው ሃገር አለን ብለው በገዛ ሃገራቸው እዚሁ የሚያርፉበት ድንኳን አካባቢ ኢትዮጵያውያን ነን የሚሉ ወገኖች ከ30 ብር በማይበልጥ ዋጋ የሚሸጠውን ሲም ካርድ በ60 ብር ሲቸበችቡላቸው ነበር፡፡ እኛ ራስ በራሳችን ካልተዛዘንን የሌላ ሃገር ሰው እንዴት ነው የሚያዝንልን? እናም የድሮው መተሳሰባችን ይቀጥል እላለሁ፡፡
የስብሰባ ትዝብት 2
የሆነ ስብሰባ ተሳትፌ ነበር እና ፅሁፍ አቅራቢው መድረክ ላይ አይኑን ላፕ ቶፕ ላይ ተክሎ በፕሮጀክተሩ ለእኛ እያሳየ ይገኛል፡፡ ካሜራ ማኑ ካሜራውን ብልጭ ሲያደርግ ይደነግጥና ንግግሩን አቋርጦ አይኑን ወደ ካሜራ ማኑ ያዞራል፡፡ ከልማድም ልማድ አለ፤ እንዲህ ዓይነት ልማድ ግን አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ መቼም ከህዝብ ፊት ሆኖ መድረክ መምራትን የመሰለ ታላቅ ጥበብ የለም፡፡ ምክንያቱም የሁሉም ሰው ዓይን እሱ ጋ ነዋ የሚያፈጠው፤ አፍጥጦም አይቀርም የሆነች እንከን ካስተዋለ ሂስ እና አቃቂር ማውጣቱ አይቀርም፡፡ ግን የዚህ ሰውዬ ሁኔታ ከሁሉም የተለየ ነው፤ አንዴ ብቻ አይደለም ፅሁፉ እስከሚያልቅ ድረስ እኮ ነው፡፡ እናም ጠረጠርኩ “ምናልባት ይህ ሰውዬ ጦር ሜዳ ያሳለፈ ይሆን እንዴ? አልያም ደግሞ አንድ ቤተሰቡን በመብረቅ አጥቷል፡፡” እሱማ በህይወት አለ፡፡
Friday, November 29, 2013
ስለ ኤግዚቢሽን…
ሚሊኒዬም አዳራሽ የተካሄደ የኮንስትራክሽን እና ፈርኒቸር ኤግዚቢሽን ነበር፡፡ እና ቅዳሜ ዕለት ጓደኛዬ ጋር ወደዛው እናመራለን፡፡ አንድም በትክክል ስለራሱ ድርጅት እና ምርት የሚያስተዋውቅ ሰው ይጠፋል? በየካውንተሩ ሄድን ግን አንዱ ሲፈልገው ዝም ብሎ ይገለፍጣል፤ የሱን ጥርስ ማዬት የናፈቀን ይመስል፡፡ ሌላው ለንቦጩን ጥሎ ፀጥ ብሎ በራሱ የሃሳብ ማዕበል ውስጥ ይጓዛል፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ ኤግዚቢሽን ለሀገሪቷ ለምን ጠቀማት? እኔ መቼም እስከማውቀው ኤግዚቢሽን ላይ እንዲሳተፉ የሚፈቀድላቸው ኩባንያዎች የተሻለ አገልግሎት ወይም ምርት ያላቸውና የገበያ ዕድል እንዲያገኙ የሚያስችል፣ ቀጥታ ከተገልጋዮች ጋር የሚገናኙበት እና ስለ ኩባንያቸውም የሚያስተዋውቁበት ነው፡፡ ይህ ሆኖ እያለ ግን የሚታየው ነገር የተገላበጠ ነው፡፡
ፉገራ
እኛ ሰፈር ፍቅረኛሞች አሉ እና ሴቷ በጣም ረዥም ሆና በተቃራኒው ደግሞ ወንዱ አጭር ነው፡፡ መቼም ፍቅር እንኳን ቁመት ሌላም ነገር የማይወስነው ጠንካራ ኃይል ያለው ቁርኝት እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ እናም ለምን ተፋቀሩ ብዬ የሞኝ አፌን አልከፍትም፡፡ ግን እንዲሁ ለመቀለድ ያህል የሰፈር ልጆች ምን ቢሉ ጥሩ ነው? “በቁመት ስለማይደራረሱ አብረው ቁመው እንኳን በስልክ ነው የሚነጋገሩት” ብለው ቁጭ፡፡ የኛ ሰው መቼም አቃቂር ለማውጣት የሚችለው የለም፡፡ እነሱ ተመቻችተው ነው እየኖሩ ያሉት፡፡ እኔ ግን ስላሳቀኝ ለናንተም ልንገራችሁ ብዬ ነው የፃፍኩት፡፡
Tuesday, October 29, 2013
ስለ ዳና ድራማ ክፍል 24
ዳና ተከታታይ የቴሌቪዝን ድራማ መተላለፍ ከጀመረ እነሆ 2ኛ ምዕራፍ፤ 24ኛ ክፍል ላይ ደርሷል፡፡ እና በዚህ ክፍል “አይዳ” የተባለችው ገፀ-ባህሪ “እቴቴ” ከተባለችው ጋር በሚያደርጉት የስልክ ቃለ-ምልልስ ላይ “አይዳ” የተቀመጠችበት ፊት ለፊት የሚገኘው ጠረጴዛ ላይ አስተውላችሁ ከሆነ የተዘቀዘቀ የኢትዮጵያ ባንዲራ ወይም ሲዘቀዘቅ የሴኔጋል የሆነ ባንዲራ ይታያል፡፡ ይህ በቀላሉ ታይቶ ችላ የሚባል ነገር አይደለም፡፡ እኔ ትንሽ ስህተት አይቼ ለማጣጣል ሳይሆን፤ ቁጥር ከአንድ ይጀምራል፣ ስህተትም እንዲሁ ከትንሽ ነው የሚጀምረው ብዬ ስለማምን ነው፡፡ ይህ ፕሮግራም በዓለም ዙሪያ የሚተላለፍ እንደመሆኑ መጠን ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ሰዎች የኢትዮጵያ ባንዲራ እንደዛ ሊመስላቸው ይችላል፡፡ ለማንኛውም ከዳይሬክተሩ ጀምሮ እስከ ተራው አርቲስት ድረስ እንደዚህ ዓይነት ነገሮችን በትክክል አስተውለው መስራት አለባቸው ባይ ነኝ፡፡ ይህ የሚመጣው ቸልተኛ ከመሆንና ለስራው ትኩረት ካለመስጠት ይመስለኛል፡፡ ምንም እንኳን በዘርፉ ባለሙያ ባልሆንም ካሜራ የሚይዘውን ቦታ ሁሉ በጥንቃቄ ማስተዋል ያስፈልጋል፡፡ ለዚህም ነው እኮ ኢዲቲንግ ያስፈለገው፡፡ በእርግጥ ተከታታይ ድራማ መስራት አሰልቺ እንደሆነ እሰማለሁ፡፡ ነገር ግን ስራዬ ተብሎ ከተያዘ የሚያቅት ነገር የለም፡፡ ይህን በአጋጣሚ አነሳሁት እንጂ በሚወጡት ፊልሞች ሁሉ አቃቂር ማውጣት ቀላል ነው፡፡ ከካሜራ ጥራት ጀምሮ እስከ ድምፅ ጥራት እንደዚሁም በታሪክ ፍሰታቸው እዚህ ግቡ የማይባሉ ፊልሞች ይወጣሉ እኮ፡፡ ይህን ከማድረግ አራት፣ አምስት ዓመት ፈጅቶ በጥንቃቄ ጥራት ያለውና ሃገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያስጨበጭብና ለኦስካር የሚታጭ ፊልም መስራት አይሻልም ወይ?
Tuesday, October 22, 2013
የመዲናችን ህንፃዎች የወል ባህሪ
“አዲስ አበባ፣
ዳርዳሯ አበባ፣
ውስጧ ሌባ፡፡”
የተባለላት አዲስ አበባ፤ ዋና ከተማ የሆነችበትን ጊዜ ለመቁጠር ወደኋላ አፄ ሚኒልክ የነገሱበትን ጊዜ ማስላት ያስፈልጋል፡፡ የዛን ጊዜ እቴጌ ጣይቱ እንጦጦ ላይ ሆነው ቁልቁል ሲመለከቱ ደስ አለቻቸውና “አዲስ አበባ” ብለው ሰይመው መኖሪያቸውን ወደዚህች ከተማ አዛወሩ፡፡ እነሆ ከዛን ጊዜ ጀምሮ አዲስ አበባ ቀስ በቀስ በእድገት ጎዳና ላይ ትገኛለች፡፡ ፎቅ መሰራት የተጀመረው በቅርብ ጊዜ ቢሆንም፡፡ ያን ሁሉ አልፋ አሁን ከተማዋ የፎቆች ውድድር የሚካሄድባት ይመስላል፡፡ ከወር በኋላ ቆይተህ የሆነ ሰፈር ብትሄድ አዳዲስ ፎቆች በቅለው ነው የምታገኘው፤ መንገድ የተሳሳትክ እስከሚመስልህ ድረስ ማለት ነው፡፡ እና አብዛኛዎቹን ፎቆች የሚያመሳስላቸው አንድ እውነታ አለ፤ ይኸውም የመስታውት ብዛት ነው፡፡ ፎቅ ያለመስታውት የማይሰራ ይመስል፡፡ ባለቤቶቹም የሚፈልጉት፣ አርክቴክቸሮቹም ዲዛይን የሚያደርጉት ተመሳሳይ ነገር፤ መስታውት በመስታውት የሆነ ቤት ነው፡፡ እኔምለው መስታውት እርካሽ ነው እንዴ? ከብሎኬት ጋር ሲነፃፀር፡፡ ለማንኛውም ይህን ስሌት ለመሃንዲሶች እንተወውና እንለፍ፡፡ ይህ የመስታውት ብዛት ከተማዋን ምድረ-በዳ እያደረጋት ነው፡፡ ምን ለማለት ፈልጌ ነው የመስታውቱ ነፀብራቅ ፊት ላይ ሲያርፍ ያቃጥላል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ እርግጠኛ ነኝ እስካሁን የዓይን ብሌኑ የተቃጠለ ሰው ይኖራል፡፡ ቤት ይቁጠረው ብለን እንተወው እንጂ፡፡ የመስታውት በረሃ ዋጠን እኮ ምን ይሻላል ትላላችሁ? ለዚህ ማስተማሪያ የሚሆን ማንኛውንም ፎቅ የሚያስንቅ ያየሁት ፒያሳ ላይ ያለው “እናት ህንፃ” ብቻ ነው፡፡ ሌሎቹ ሁሉም አንድ መሃንዲስ ዲዛይናቸውን የሰራቸው ይመስል ተመሳሳይ ናቸው፡፡ እኔምለው ዲዛይን ያለመስታውት አይቻልም አያምርም ያለው ማነው? ለማንኛውም መንግስትም የድርሻውን ቢወጣና ዓይናችን ከመጥፋቱ በፊት መፍትሄ ቢያፈላልግ፤ ባለሙያዎቹም ሙያቸውን የሚያሳድግ ነገር ቢሰሩ መልካም ነው እላለሁ፡፡
Friday, October 18, 2013
የጨዋታ መልስ ድባብ
የኢትዮጵያ እና የናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ ዕለት ማታ የአልኮል ገበያ ደርቶ ነበር፡፡ ለምን መሰላችሁ፤ መቼም የኛን ሀገር ነገር ከኔ የበለጠ ታውቁታላችሁ፤ ስናሸንፍ ለደስታ ተብሎ መጠጥ ቤት፤ ግብዣ በግብዣ፡፡ ስንሸነፍም እንደዚሁ ለንዴት ማስወገጃ ተብሎ መጠጥ ቤት፡፡ እና የአሁኑ ደግሞ ኢትዮጵያ ትሸነፋለች ብለው ቁማር ያስያዙ አገር ወዳድ ያልሆኑ የናይጄሪያ ደጋፊዎች በደስታ ጮቤ ረግጠው መጠጥ ቤት ያሳልፋሉ፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ኢትዮጵያ በመሸነፏ ቅስማቸው የተሰበረ ንፁህ የኢትዮጵያ ደጋፊዎች እና ኢትዮጵያ ታሸንፋለች ብለው የቆመሩትም ጭምር ንዴቱን ለመርሳት ብለው መጠጥ ቤት ከትመው ነው ያመሹት፡፡ እና በዚህ መሃል የሃገሪቷ የመጠጥ ፍጆታ ከፍ ሳይል አይቀርም ብዬ እጠረጥራለሁ፡፡ የሃገሪቷ GDP በዚህን ያህል ምጣኔ ባያድግም በዕለቱ፡፡ በመሸነፋችን ላዘናችሁ ኢትዮጵያውያን በመልሱ ጨዋታ እናሸንፋለን አይዟችሁ እላለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ትሸነፋለች ብላችሁ ቁማር የበላችሁ ሟርተኞችም ልብ ይስጣችሁ፤ ተመሳሳይ ይሆናል ብላችሁ እንዳትሸወዱ፡፡
Thursday, October 17, 2013
የስም መመሳሰል ወይስ የስም መገለባበጥ
ሰሞኑን አንድ የገጠመኝን ልንገራችሁ፡፡ ሜክሲኮ አካባቢ ነው፡፡ አንድ ከክፍለ ሀገር የመጣ ልጅ ከአውቶብስ ተራ ተነስቶ ታክሲ ይዞ ሜክሲኮ ደርሷል፡፡ እና ወደ ለገሃር እያመራ እያለ እኔጋ ተገናኘንና “የሞጆ መንገድ ወዴት ነው” ብሎ ጠየቀኝ፡፡ እኔም ሞጆ ከአዲስ አበባ ውጪ እንደሆነና ሚኒ ባስ ይዞ ወደ ደብረዘይት መሄድ እንደሚችል ስነግረው፡፡ “ሞጆ ኮንዶሚኒየም ያለበት” ሲለኝ ነቄ ብዬ “ጀሞ ኮንዶሚኒየም ማለትህ ነው” አልኩት፡፡ በዚህ ጊዜ ልጁ “አዎን” አለ፡፡ ከዛ ታክሲ መያዣውን አሳየሁትና እብስ አልኩኝ፡፡ አስቡት እስኪ ከአውቶብስ ተራ ለገሃር ድረስ የመጣው የሞጆ ታክሲ ሊይዝ ነበር፡፡ እዛ ደርሶ ያው መመለሱ አይቀርም ነበር፡፡ አሁን ይኼ “የስም መመሳሰል” ነው ወይስ “የስም መገለባበጥ”፡፡
Wednesday, October 2, 2013
Tuesday, October 1, 2013
Tablets without teachers improving literacy in Ethiopia
By Julia Brakel
Laptops and tablets are in everyday use as much in Addis Ababa as elsewhere on the African continent, with the city’s cafes crammed with people working, updating their Facebook profiles or simply surfing the Web.
However, the technology is now also being used in one of Ethiopia’s more remote rural areas. As part of a radical new system, it is hoped will improve literacy amongst children. The village of Wonchi is reached from the Ethiopian capital by a two-and-a-half hour westward drive followed by a lengthy trek on foot.
Its inhabitants live without electricity or running water. But here in the central Ethiopian highlands within the volcanic caldera of the same name, the children of Wonchi are learning to read and write using some of the latest technology available. Abebech’s finger glides over the dusty tablet in its brown leather case. Many of the letters have been mixed up and the nine-year-old’s task is to mark the hidden English words with her finger.
She quickly finds cat, dog and brother. The computer rewards her for her endeavours by replying “awesome!” “I carry the tablet with me everywhere I go, whether I am at home or outside looking after the animals,” says Abebech, who often has to help her impoverished family tend to their cows and sheep.
The young girl is one of 40 children to have received a learning tablet in February 2012 as part of a two-year research project devised by scientists from the Massachusetts Institute of Technology (MIT), Tufts University near Boston and the University of Georgia.
Half of the children are from Wonchi where the literacy rate is virtually zero with the other half from a small village not far from the town of Wolenchite. None of the children had ever attended school before receiving their tablets.
The researchers wanted to find out what happens when children are given early literacy apps and games without receiving any operating instructions or tuition in their use. The results have stunned the scientists. They found that children between the ages of 4 and 10 quickly learned not only how to turn the solar-powered tablets on and off but also what the function of the installed early learning apps was.
Most of the children now understand the English alphabet and can read and write words. Ethiopian project manager Michael Girma visits the village once a week to collect the data from tablets’ chips which is then sent to the United States for analysis. In this way, the scientists can see exactly how often each of the apps are opened and with what results when it comes to improved literacy.
“It is normally necessary to build a school and employ a teacher to teach children how to read and write,” explains the 29-year-old IT expert, who studied computer science in Addis Ababa and Helsinki. “But this simply isn’t possible in many of the world’s more remote regions.”
Girma believes the learning tablets offer a promising educational technique for the future, which appears to be backed up by the progress made by the children of Wonchi. Maryanne Wolf, one of the leading scientists at Tufts University, is also delighted with the progress made by the English language students.
“We believe that once the children have achieved a basic level of literacy they will be able to learn everything else and in a position to greatly increase their level of knowledge,” she explains.
Unfortunately, the project is scheduled to finish this year and it remains unclear how and if tuition for the children of the caldera will continue. All the children involved in the programme are eager to continue learning but the nearest primary school is a two-hour walk away. Abebech’s thirst for knowledge certainly has not been sated and the youngster has already chosen a future career for herself.
“I want to become a teacher and give lessons to the other children in Wonchi,” she says before turning her eyes back to her tablet. – DPA
Monday, September 30, 2013
Thursday, September 26, 2013
Monday, September 23, 2013
አነጋጋሪዋ የአንድ ብር ኖት
የኢትዮጵያችን የወረቀቱ አንድ ብር ኖት ለየት ያሉ ባህሪያት አሏት፡፡ ከነዚህም ውስጥ አነበሳው ሲያገሳ፣ እረኛው ሲስቅ፣ በሬዎቹ ሲራመዱ፣ ወፎች ሲዘምሩ፣ የአባይ ፏፏቴ በግርማ ሞገሱ ሲፈስ፡፡ ብቻ ምን አለፋችሁ ብዙ ድምፆች የሚንጫጩባት ብቸኛ ብር ናት፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በጣም የሚገርመው ነገር ከአንድ ብር አቅም 13 ጊዜ አንድ ብርነቷን የሚያሳብቁ ፅሁፎች (በፊት ገፅ 7 ጊዜ እና በጀርባ 6 ጊዜ) አሏት፡፡ የፊትአውራሪ የሆነው መቶ ብር እንኳን 10 እሱነቱን የሚገልፁ ፅሁፎች ብቻ ነው ያሉት፡፡ አሁን አንድ ብር ላይ ይህን ያህል የመግለጫ ዝባዝንኬ ማብዛት ምን ይባላል፡፡ ደግነቱ ይህች ብር ወደ ሳንቲም ለመቀየር እየተጓዘች ያለች በመሆኗ ብዙ የሚያጨቃጭቅ ባይሆንም የሆነ ሚስጥር ግን ያላት ይመስላል፡፡ ምናልባት ብ ሰው የሚጠቀምባት በመሆኗ ይሆን? ለማንኛውም ብሔራዊ ባንክን መጠየቁ አይከፋም፡፡
Friday, September 20, 2013
አበባዮሽ…
አበባዮሽ የለም (2X)
መብራቱ አለ? የለም…በየሰፈሩ የለም፥
ውሀውስ አለ? የለም…በየሰፈሩ የለም፥
ኔትዎርኩስ አለ?…በየሰፈሩ፥
መንገዱስ አለ? …በየሰፈሩ፥
ታክሲውስ አለ?… በየሰፈሩ፥
ዋይ ዋይ
ድንቄም ሙዳይ፥ ከብለል በይ (2X)
የራበው አለ? የለም …በየመንደሩ የለም
የከፋው አለ? የለም …በየመንደሩ የለም፥
ለሙት ዓመቱ፥… ችግኝ ትከሉ፣
ዲሽ የሌላቸው…ሰዎች ተጉላሉ፤
ጧት ማታ አዩ፥… ችግኝ ሲተክሉ፥
አበባ ይበቅላል…በየገጠሩ
ውጭም ተልኳል…ተሳክቶ ምርቱ
ዋናው ዶላር ነው….ስንዴ የት አባቱ።
ዋይ ዋይ
የእህል ሙዳይ ከብለል በይ (2X)
አ ብለን መጣን አ ብለን (እያዛጋን)
ሚበላ አለ ብለን።
ኡ ብለን መጣን ኡ ብለን (እየጮህን)
ቀባሪ አለ ብለን።
የእድርተኞች ቤት የለም ካቡ ለካቡ የለም
እንኳን ውሻቸው…. ሞቶአል እባቡ።
ዋይ ዋይ
የእንባ ሙዳይ ኮለል በይ። (2X)
በሉ ልጆቼ የለም ብሉ በተራ፤ የለም
ቤት ያፈራውን….ደረቅ እንጀራ፤
ተደራጅቼ፣… ወጥ እስክሰራ።
እንኳን ወጥና፣…. የለኝም ኩሽና፣
ስዞር አድራለሁ፣… ቁራሽ ስጠና።
ዋይ ዋይ
የእንጀራ ሙዳይ ከብለል በይ። (2X)
የደመወዝ ለታ የለም የአስቤዛው የለም
ቫቱን አስልቼ፣…. ደላድዬው፣
የ20/80ው፣…. ጎኔን አለው።
ከጎኔ ጎኔ፣…. ኪሴን ኪሴን፤
ወዳጄን ጥሯት፣…. ውሽማዬን፣
እርሷም ከሌለች፣….ኮማሪቷን፣
እንፈፅማለን፣… ራዕይውን፣
እናሳካለን፣… ሌጋሲውን፣
ከዚያም አበሉን… ተሰብስበን።
ዋይ ዋይ
የእጦት ሙዳይ ኮለል በይ። (2X)
መጣልኝ ብለሽ፣….ብትሞነጭሪ፣
ብትራቀቂ፣….ነሽ አሸባሪ።
ከእጮኛ ጋር …ቡና ብትጠጪ፣
በዚያው እደሪ፣ ቤት እንዳትመጪ
ዋይ ዋይ
የክስ መዝገብ ገለጥ በይ። (2X)
ቅዳሜ መጥቶ …ልዘይረው፣
ጋዜጣ ብሻ፣… የት ላግኘው?
ፉክክር ገባ፥… ሰልፍ ብጠራ፥
ፈቃዴን ነጥቆ፥… እርሱ አሰማራ፥
በሰልፉ ዋዜማ፥… ተንኳኩቶ በሩ፥
ሄጄ ማነው ስል፥… ሰልፍ እንዳትቀሩ፥
ዋይ ዋይ
የጉድ ሙዳይ ኮለል በይ። (2X)
ከብረው ይቆዩ ከብረው
በዓመት አንድ ልጅ ሰድደው፣
በቀን ሶስት ጊዜ በልተው፣
ልጅ ትምህርት ቤት ልከው፣
ከሙሰኛ ጅብ ተርፈው፣
ከበሮት ውሃ ቀድተው፣
መብራት ሳይሰጉ አብርተው፣
ለታክሲ ግፊያ ትተው፣
ቀንቶት 40/60ው፣
ጋዜጣ ሸጠው፣ ገዝተው፣
መሳቀቁንም ትተው፣
ሃሳቦትንም ገልፀው፣
የታሰሩቦት ተፈተው፣
የወደዱትን መርጠው፣
ቻናል ቀያይረው አይተው፣
በሃቅ ነግደው አትርፈው፣
ግብሩን በልኩ ከፍለው፣
ከብረው ይቆዩ ከብረው።
ከብረው ይቆዩ በደግ (2X)
የወለዱት ልጅ ይደግ።
ከብረው ይቆዩ በፏፏ (2X)
የወለዱት ልጅ ይፏፏ።
ይሸታል ጠጅ ጠጅ (2X)
የኢትቪዮጵያ ደጅ።
የሸታል ሽሮ ሽሮ (2X)
የማምዬ ጓሮ።
/ዮሐንስ ሞላ/
Tuesday, September 17, 2013
አማርኛ በባህርዳር
ለስራ ጉዳይ ከተለያዩ ሰዎች ጋር ወደ ባህርዳር ከተማ ሄጄ ነበር፡፡ ታዲያ ከመካከላችን አንዱ የደቡብ ክልል ተወላጅ በመዲናዋ ከሚገኙ አንድ ጎዳና ላይ “ተቋማት” ተብሎ መፃፍ የነበረበት ቃል “ተቆማት” ተብሎ ተፅፏል፡፡ ለዛውም የአማራ ክልል መዲና በሆነቸው በውቢቷ ባህርዳር ከተማ፤ የሆነ ቢል ቦርድ ላይ ማለት ነው፡፡ እና ምን ቢል ጥሩ ነው? “ለምንድን ነው እንደዚህ የሚፃፈው እኔ እኮ አባቴ ሳይማር ያስተማረኝና አማርኛን በትውልድ ሳይሆን በትምህርት ያወቅኩ ሰው ነኝ፡፡ ስለዚህ እንደዚህ መፃፉ ይከነክነኛል፡፡” አለ፡፡ እኛም ገርሞን ተሳሳቅንና “ከደቡብ ክልል መጥተህ እዚህ አማርኛ በተወለደበት ቦታ ኢዲተር መሆን አማረህ” ብለን ቀለድንበት እና በደንብ ተሳሳቅን፡፡ ግን እኮ ይህ ዓይነቱ ስህተት በየቦታው ነው ያለው፡፡ ታላላቅ ዝግጅቶች እንኳን ሲዘጋጁ የሚፃፉ ማስታወቂያዎች፣ ቢል ቦርዶች፣ በራሪ ፅሁፎች ላይ እራሱ ስህተት ይታያል፡፡ የሚገርም እኮ ነው፡፡ ምናልባትም እንግዲህ ይህ ዓይነቱ ስህተት የሚመጣው ፀሃፊው ዲቃላ ፊደል የመፃፍ ችሎታ ስለሌለው ወይም ደግሞ “ዲቃላ” የሚለውን ቃል በመፍራቱ ሊሆን ይችላል፡፡ እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው በተለይ ብዙ ሰው የሚያነባቸውን ፅሁፎች በደንብ ትኩረት ሰጥተናቸው አርመን ከልሰን ከጨረስን በኋላ ለተጠቃሚ ብናደርሳቸው ይሻላል ለማለት ያህል ነው፡፡
Friday, August 23, 2013
ጎረምሳው ልቡን ያሻፈተችውን ቆንጆ ለሚስትነት ለመጠየቅ አባቷ ቤት ይሄዳል::
......
አባት:- ልጄን ለጋብቻ ልትጠይቅ መጥተህ በአጠገቤ ማስቲካ ታኝካለህ ትንሽ እንኳን አታፍርም? ክብረቢስ
ጎረምሳው:-ይቅርታ ጌታዬ ስለጠጣው አፌ እንዳይሸት ብዬ ነው
አባት:-ጭራሽ መጠጥም ትጠጣለህ?
ጎረምሳው:-አዎ ግን አልፎ አልፎ ናይት ክለብ ስሄድ ብቻ ነው ምጠጣው
አባት:-ናይት ክለብ ስሄድ ብቻ?!! አታፍርም እንዴ ልጄን ለመጠየቅ ስትመጣ?
ጎረምሳው:-ከእስር ቤት ስወጣ ነው መሄድ የጀመርኩት እንጂ በፊት አልሄድም ነበር
አባት:-የባሰ አታምጣ!!!አንተ ሌባ ልጄን ሰርቀህ ልታበላት ነው እንዴ?
ጎረምሳው:-ሌባ አይደለሁም ሰው ገድዬ ነው እስር ቤት የገባሁት
አባት:-ምን!!!! ነብሰ ገዳይ ነህ?
ጎረምሳው:-አይደለሁም የዛን ቀን በጣም ተናድጄ ስለነበር ነው ሰውየው የኛ ጎረቤት ነበር ልጁን ለማግባት ጠይቄው ከለከለኝ ከዛ ገደልኩት::
አባት:-ና እስቲ ልጄ ና እቀፈኝ ለልጄ እንዳንተ አይነት ጥሩ ባል ነበር ስፈልግ የነበረው
ወይ የሰው ነገር
ፍርድቤቱ ጥቅጥቅ ብሎ ሞልቷል፤ ተከሳሹ በሀፍረት አቀርቅሮ ቆሟል፤ ዳኛው ጥቁር ካባቸውን ደርበው ተሰይመዋል፤ ችሎቱ ውስጥ የውጥረት ፀጥታ ሰፍኗል…
ዳኛው ክሱን ማንበብ ጀመሩ
“እንግዲህ የመጀመርያው ክስህ ባለቤትህን በመዶሻ ግንባሯ ላይ ደጋግመህ በመምታት ገለሀታል የሚል ነው…”
በድንገት ከፍርድቤቱ የጀርባ ወንበሮች አካባቢ “ከይሲ! አረመኔ!” የሚል ድምፅ ተሰማ
ዳኛው ክሱን ማንበብ ቀጠሉ
ሁለተኛው ክስ ደሞ የባለቤትህን እናት በመዶሻ በአሰቃቂ ሁኔታ ገለሀል በሚል ነው
አሁንም ከሗላ በኩል “አፈር ብላ! አረመኔ!” የሚል ድምፅ አስተጋባ
ይሄኔ ዳኛው በጣም ተበሳጩና፤ ማነው እንደዚህ ችሎቱን የሚበጠብጠው ፤ እስቲ ወደፊት ተጠጋ! ብለው አስጠሩትና ለምን እነዚህን ነገሮች እንደተናገረ ጠየቁት
ሰውዬውም ዳኛው ፊት ቀርቦ እንዲህ ብሎ መለሰ:-
"አሁን የተከሰሰው ሰውዬ ለ15 አመት ያህል ጎረቤቴ ነበር፤ ባለቤቱን እና አማቹንም አውቃቸዋለሁ ፤ ይሄ ሁሉ አመት ስንኖር ለአንዳንድ ስራዎች ፈልጌ መዶሻ እንዲያውሰኝ ስጠይቀው ሁልጊዜ የለኝም ነበር የሚለኝ … አሁን መዶሻ እያለው እንደከለከለኝ ስለገባኝ ተበሳጭቼ ነው፡፡
Source: www.fb/amanuelhospital
Saturday, August 10, 2013
እስክርቢቶ የዋጠው ልጅ
እናት በቅርቧ ወዳለው ሆስፒታል ድንገተኛ ክፍል ስልክ ትደውላለች፡፡
ነርስ፡- “ሀሎ፤ ምን እንርዳዎት?”
እናት፡- “አረ በነፍስ ድረሱልኝ! ልጄ ድፍኑን እስክርቢቶዬን ዋጠብኝ”
ነርስ፡- “እሺ አሁኑኑ እርዳታ የሚሰጥ አምቡላንስ እንልክልዎታለን”
እናት፡- “አምቡላንሱ እስኪመጣ እኔ ምን ላድርግ ታዲያ?”
ነርስ፡- “እስከዚያው በእርሳስ ይፃፉ”
ተወደድኩ ባይ
ልጃገረድ፡- “ታቃለህ አንተን ባየሁ ቁጥር አንድ ትልቅ ሰው ትውስ እንደሚለኝ?”
ተወድጃለሁ ባይ፡- “ውይ ታድዬ ማነው ግን የኔ ቆንጆ?”
ልጃገረድ፡- “ሳይንቲስቱ ቻርለስ ዳርዊን”
ተወድጃለሁ ባይ፡- “እንዴ! እኔ ከርሱ ጋር በመልክ ሆነ በቁመና አልመሳሰል፤ በችሎታ አልመጣጠን፤ እንዴት ሆኖ ነው እሱ ትዝ የሚልሽ የኔ ቆንጆ?”
ልጃገረድ፡- “መጀመሪያ ሰው ከዝንጀሮ ነው የመጣው ያለው እሱ አልነበር?”
የሰካራም ነገር
አንዲት ያለአቅሟ ጠጥታ በመጠጥ ድንባዧ የጠፋ ሴት ፖሊስ ጣቢያ ስልክ ትደውልና “የመኪናዬ ዕቃ በሙሉ ተዘርፏልና ድረሱልኝ” ስትል ታመለክታለች፡፡
ተረኛ ፖሊስም የተሰረቀባትን ዕቃ በቅድሚያ እንድታስመዘግብ ሲጠይቃት “መሪው፣ የእጅ ፍሬኑ፣ ማርሹ፣ ፍሪሲዮን፣ የእግር ፍሬንና ነዳጅ መስጫው ሁሉ እንደሌለ” ተናገረችና ስልኩን ዘጋችው፡፡
ከደቂቃዎች በኋላ ሴትየዋ ትንሽ ስካሯ ሲበርድላት ወደ ፖሊስ ጣቢያው መልሳ ትደውልና ለፖሊሱ “ይቅርታ ጌታዬ በስህተት በመኪናዬ የኋላ በር ገብቼ ነው እንጂ ሁሉም ነገር ስላለ በቃ ተውት” ብላቸው እርፍ፡፡
Wednesday, July 31, 2013
ሶስት ብርጭቆ…
አንድ ሰውዬ ሁልጊዜ ወደ ቡና ቤት ጎራ ሲል አንድ ዓይነት መጠጥ በሶት የተለያዩ ብርጭቆዎች በማዘዝ ፊት ለፊቱ ደርድሮ በየተራ ከሶስቱም እየተጎነጬ ነው የሚጠጣው፡፡ ታዲያ ይህ ከሰው ለየት ያለ ባህሪው የሚያስገርመው የመጠጥ ቤቱ አስተናጋጅ አንድ ቀን “ይቅርታ ወንድሜ! ሁልጊዜ አንድ ዓይነት መጠጥ በሶስት ብርጭቆ እያዘዝከኝ ሁሉንም የምትጠጣው ግን አንተው ነህ፤ ከዚህ ሁሉ አንዱን ጠጥተህ ስትጨርስ ሌላውን ባመጣልህ አይሻልም?” ሲል ይጠይቀዋል፡፡
ሰውዬውም “የለም! የለም! አየህ ይህ ትልቅ ምክንያት አለው፤ አንዱ ብርጭቆ የኔ ድርሻ ሲሆን፤ ሁለቱ ግን ለስራ ፊልድ የሄዱ በጣም የምወዳቸው ጓደኞቼ ድርሻ ነው፡፡ ስለዚህ እነሱን ለማስታወስ ስል ነው በሶስት ብርጭቆ አዝዤ የምጠጣው” ሲል ይመልስለታል፡፡
ታዲያ አንድ ቀን ይህ ሰውዬ ያለወትሮው ሁለት ብርጭቆ መጠጥ ብቻ ቢያዘው አስተናጋጁ ግራ በመጋባት “ውይ ዛሬ ምነው ሁለት ብቻ አዘዝከኝ? አንዱ ጓደኛህ ሞተ እንዴ?” ሲል ይጠይቀዋል፡፡
ሰውዬውም “የለም የለም ሁለቱም ደህና ናቸው፤ እኔ መጠጥ ስላቆምኩ የራሴን ድርሻ ቀንሼ ነው” ብሎት እርፍ!!
Thursday, July 25, 2013
ለካስ…
Saturday, July 13, 2013
People around the world surprised that Ethiopia has Airline [Reactions from DailyMail -UK , CNN and Twitter]
After the news that Ethiopian airlines plane caught on fire was covered by international media, instead the of the main news, many people were surprised to learn that Ethiopia has airline and owns the most advanced plane in the world.
Here are the reactions from CNN and Twitter.
We will update it as we get more reactions.
DailyMail
Boeing Dreamliner of Ethiopean Airlines? I thought the place was all desert and famine.
I thought Ethopia was a poor country how the hell could they afford to buy one of these planes?
Ethiopia? Thought their people were starving, it's akin to someone claiming benefits and turning up in a Rolls Royce!
Huffingtonpost
I work in aviation, have for the last 15 years, and mainly work International assignments at this point. How Ethiopian Airlines can afford a 787 and also get to the point in the waiting list where they already have on is beyond me.
Ethiopian Airlines? They probably swapped out the batteries with some they bought from K-Mart (on layaway).
teve Klingensmith • 3 hours agowhy does Ethiopia have an airline when all the people there are starvingGhost Rider • 6 hours agoThe bigger news is that Ethiopia can afford Dreamliners.
Reactions from CNN
TrayvonKardashan • an hour ago
Ethiopian have an airplane? They barely eat food!
i did not know ethiopia has airplanes.
Wow Ethiopia can afford a Dreamliner...now that is amazing. I wonder if Obama gave it to them.
coment8r southernwonder • an hour ago
a lot of us are stuck in the bloated belly past - Ethiopia has evolved
No real facts, or news for that matter...maybe the Ethiopians built a campfire in the plane and were roasting a goat..
I thought flying in Ethiopia meant flapping your arms in a tribal feather dress.
johnsmith9875 SirOinkers • 2 hours ago
I hate flying Air Ethiopia. Meals are never served, ever.
Ethiopian Airlines? Some dude probably left a hooka going in the galley.
What shocks me is that there are enough people coming and going to Ethiopia to require a Dreamliner.
HeavyCavalrySgt • 12 minutes ago
I am a little surprised that Ethiopian Airlines operates 787s. I didn't realize that, but it looks like they own almost 10% of the fleet.
"The fire ignited on an empty 787 operated by Ethiopian Airlines that was parked at London's Heathrow airport."
I find this statement disturbing. This is a country which still holds the highest number of citizens who are literally starving to death, yet can afford the latest in commercial aircraft.
GodIs JustAnIdea Knightmario • 37 minutes ago
Ethiopian is a private airline company and their customers are Americans and European who go to Ethiopia to steal all the natural resources and have sex with local prostitutes, which are very cheap over there yet quite hot ...
so see, it's not the country .. we pay for the airplane ...
J.tell GodIs JustAnIdea • 28 minutes ago
Ethiopia doesn't have a lot of natural resources. And it's hard to call something "stealing" when you have a buyer and a seller agreeing upon a price. I'll need to check out the prostitute thing first hand and get back to you, though the Ethiopian chicks in the DC metro area are hot, but not cheap.
GodIs JustAnIdea J.tell • 24 minutes ago
well, see, this is what you do not know of the Ethiopians .. they are indeed very smart, at least those who got an education, which is very hard to get in Ethiopia
With regards to the babes .. they are among the most beautiful women in history ... of course ... it's Africa so sex is a dangerous business
Oh natural resources .. dude .. Ethiopia has no oil, but tiny rocks you can make into expensive thing women will want you to buy for them
J.tell GodIs JustAnIdea • 19 minutes ago
Well, I'm only having safe sex until marriage, so I am always careful. I do know a little about Ethiopia. That country's economy is growing fast now. It's also greatly expanding it's hydro power, so much so that it will be a major exporter of electricity. But the quantity of it's natural resources is not high, especially considering it's large population. It will have to depend on it's most important resources....it's people.
GodIs JustAnIdea J.tell • 17 minutes ago
unless war breaks up again, Ethiopia will be a leading country in African in 10-15 years .. just wait .. these guys are extremely smart ... so many wars selected the smartest only among the survivors
J.tell GodIs JustAnIdea • 13 minutes ago
I agree. Ethiopia's high GDP growth numbers are more sustainable over the long term than many other African countries. This will translate into a more important role for the country.
J.tell Amala ati Ewedu • 11 minutes ago
If Nigerians are smarter, they should prove it by doing something intelligent with all that oil wealth. Nigeria is a major exporter of crude oil, yet has to import most of it's gasoline. How intelligent is that?? Imagine if Ethiopia had a trillion dollars worth of oil.
Reactions from Twitter
How the hell does Ethiopia have its own airline?
year after year we are asked for charity for Ethiopia yet they can afford to have a their own airline using 1 of the most advance planes
Wtf. Ethiopia has an airline,don't expect any food on board.
The passer by white guy said "I didn't even know Ethiopia had airline." The fire at least put us on the map.
Alasdair Mackie @AlasdairMackie15m
We go on about people on benefits with big tellys and iPads but Ethiopia has Dreamliners.
Pamela Meehan @pamela_meehan17m
@ABC @ABC7 Ethiopia has an Airline? Wow the things you learn.
Ethiopa have their own airline? They should stop moaning about their Boeing Dreamliner catching fire and get some kids fed!
That Ethiopian airlines plane caught fire because it's made from sticks and mud. What did you expect?
Bryan Sargent @dampmelonballs3m
How comes Ethiopia used to have kids with flies in thier eyes now they have 2 boeing 787 dreamliners although 1 has some fire damage!
swedishmarcus @swedishmarcus47m
The most surprising thing about the news of an Ethiopian Airlines fire at Heathrow is that Ethiopia has an airline.
Friday, July 12, 2013
Wednesday, July 3, 2013
In Ethiopia, the massive Nile River dam project is compared to the story of American Hoover Dam
ASSOSA, Ethiopia — The book, a history of Hoover Dam, fell from the dashboard as Simegnew Bekele drove through the rugged mountains where the engineer is leading construction work on Ethiopia’s massive Nile River dam.
“This book,” he said, picking it up, “I am reading it now ... It’s a fascinating story. This dam too (has) a history one day someone will write about.”
Simegnew’s sentiment illustrated the great expectations of a dam that has raised tensions between this Horn of Africa nation and Egypt, which is concerned the ongoing project will diminish its share of Nile River waters. Reading the book, a gift from Ethiopians he met in New York recently, the engineer has come to see similarities between the Ethiopian dam-in-progress and Hoover Dam, the Great Depression-era project that in its time became an icon of American enterprise under difficult economic conditions.
“Hoover Dam was constructed when America was (in) depression,” Simegnew said. “It was an enormous success. I am sure our dam too will herald a bright future for this country and also for the whole region.”
Despite the concerns of Nile-dependent Egypt, Ethiopia —whose economy suffers frequent power failures —has vowed to proceed with the dam that would become the biggest hydro-electric power station in Africa. In May, Ethiopia started to divert Nile waters to make way for the $4.2 billion dam which, when it is finished, will have the capacity to produce 6,000 megawatts of electricity. Ethiopia’s national electricity corporation says potential buyers of Ethiopia’s electricity will include the two Sudans, Kenya, Djibouti, Somalia, Uganda and even wary Egypt.
In Ethiopia’s Benishangul-Gumuz region near Sudan, some 800 kilometers (500 miles) from the capital, workers labor under intensely hot conditions and gigantic machines smash boulders in order to make the dam a reality by July 2017. Even as Egyptian and Ethiopian diplomats talk over the dam’s impact on the volume of Blue Nile waters flowing to Egypt, construction work is proceeding apace here in a sign of Ethiopia’s determination to resist Egyptian pressure. Some 5,000 Ethiopians, joined by 200 expatriates from 20 nations, work in shifts 24 hours a day. Visitors here have to go through multiple security checkpoints that are manned by soldiers wearing “anti-guerrilla” tags on their fatigues. The Italian construction firm Salini is building the dam while the Chinese company Electric Power Equipment and Technology Co. Ltd. is building power lines for it.
Simegnew, the engineer, told reporters last week that some of the diverted Nile waters are accumulating in a temporary coffer dam, and officials say that the filling of the reservoir will start next year. Power lines to connect the dam’s output with the national grid are being put up, and cables from the national grid extend to Djibouti, Sudan and, later, Kenya.
“During the filling of the reservoir, which will take five to six years, we won’t have any fixed impoundment rate to make sure the water flow downstream will not be significantly affected,” Simegnew said.
Ethiopia’s Nile project has won the support of upstream countries in East and Central Africa that have been meeting under the banner of the Nile Basin Initiative, which endorsed the new Nile River Cooperative Framework Agreement. That accord, ratified last month by Ethiopia’s parliament, was conceived to replace the 1929 treaty written by Britain that awarded Egypt veto power over other countries’ Nile projects. Sudan and Egypt signed a deal in 1959 splitting the Nile waters between them without giving other countries consideration. Egyptian politicians have suggested attacks against Ethiopia to sabotage the dam, and Egyptian President Mohammed Morsi last month warned that “all options are open” to challenge the project.
Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn said last week that, while he was willing to accommodate Egypt’s concerns, the continued constructing of the dam and its size are “red lines” that will not be crossed by the negotiations.
If the dam is completed without incident, it would be a remarkable achievement for Ethiopia’s leaders who dreamed of something big and wanted an equally grand name for the dam. Originally a secret project called X, the dam was later called the Grand Ethiopian Renaissance Dam.
David Shinn, former U.S. ambassador to Ethiopia, said he doubted Egypt’s dispute with Ethiopia over the Nile River would degenerate into armed conflict.
“Following long periods of silence, there are periodic outbursts as we have seen in the past month,” said Shinn, who is now a professor at George Washington University’s Elliott School of International Affairs. “I expect this trend to continue but not to result in conflict between the two countries.”
The Ethiopian government, which secured a $1 billion loan from China for power lines for the Nile dam, says it will continue to raise more funds domestically. Government employees have for the second time paid their one-month salary to buy bonds the government is selling. Private banks are ordered by the central bank to buy bonds worth millions of the Ethiopian birr.
Yilma Seleshi of the Ethiopian Water Resource Institute says the dam would consistently bring in hard currency for at least a century, returning the massive investment it is requiring. In his study presented during a meeting at Ethiopia’s Addis Ababa University last week, he estimated that Ethiopia would earn 2 million euros in daily income from power sales to neighboring countries.
Source: http://ethioprofessionals.com
Thursday, June 20, 2013
የልብስ ማስጫ ሲጠፋ…
Sunday, June 16, 2013
Egypt - Ethiopia: Storm on the Nile
Sabotage, corruption and intimidation to hamper the construction of Ethiopia's hydroelectric dam were brought to fore as Egypt weighed its options during a crisis meeting... on television.
But Ethiopia won't be intimidated.
Ethiopia evoked the wrath of the powers that-be in Egyptian politics on 28 May, as the East African country prepared to divert water from the Nile River to test its Renaissance Dam.
Egypt believes the Ethiopian dam could affect its water supply.
On 3 June, a meeting called by Egyptian President Mohamed Morsi quickly turned into a council of war.
Some of the attendees suggested a number of actions to disrupt the construction of Ethiopia's Renaissance Dam, including destroying the infrastructure, corrupting top Ethiopian officials or even funding rebel groups.
The confabulation, transmitted live on television without the prior knowledge of the officials, reportedly, was met with rage.
In a twitter posting, Ethiopia's Foreign minister said his country won't be intimidated.
But Morsi later assured Ethiopia that his country will take no such action. One of his advisors was also quick to add that the Egyptian officials had not been warned about the live transmission of the meeting.
The construction of the $3.2bn Renaissance Dam was announced in 2011 and is part of a vast $9bn hydro-electric energy programme being undertaken by Ethiopia. Works will be finalised by 2016.
The dam is expected to generate about 6,000MW of electricity, the largest on the African continent, and could see Ethiopia becoming a net exporter of cheap electricity in countries within the sub region, including Egypt.
The Renaissance Dam is being constructed near the Sudanese border, on the Blue Nile - which meets with the White Nile in Khartoum to form the Nile river that flows through Egypt.
Despite Egypt's opposition to the dam's construction, Ethiopia argues that the Nile's downstream flow will not be affected.
Experts estimate that Egypt could see a 20 percent reduction of the Nile's downstream flow in the initial months following the opening of the dam in 2014. The filling of the dam is expected to last between three and five years.
Colonial-era agreements signed with Sudan in 1929 and 1959 saw Egypt taking an estimated annual share of 51 billion square metres and Sudan parting with an estimated 18 billion square metres, giving the two countries over 90 percent of the Nile's water.
Ethiopia says it contributes to more than 80 percent the Nile's water.
In April 2010, riparian countries of the Nile, including Ethiopia, Uganda, Rwanda, Tanzania and Kenya signed the Entebbe agreement, which stipulated the redistribution of Nile's water.
Egypt and Sudan boycotted the talks, with Egypt saying the agreement was non-binding.
But the inclusion of Burundi meant that the majority of countries on the Nile water course had assented to the agreement despite Egypt's protest.
Source: http://ethioprofessionals.com
Wednesday, June 5, 2013
Cairo and Khartoum in talks on Ethiopia Nile diversion
CNN interview with Betsegaw Tadele: Obama called him the 'skinny guy with the funny name', but who is he?
Egyptian politicians caught discussing plan to sabotage Ethiopian dam
Wednesday, May 29, 2013
Excessive Hotel Rates Annoy Foreign Diplomats
May 28, 2013 - The Ministry of Foreign Affairs for some some six month now has been consulting with hotels and restaurants not to make a sudden price increase for their services in relation to the 50th anniversary of the Organization of African Unity/African Union (AU), according to the Reporter. Unfortunately, many did increase the regular prices fourfold or more on average and quite a number of them are making millions of dollars in just about a week.
The dramatically increased prices in the hospitality industry especially for room and related services, annoyed not only the diplomats members who are accustomed to the regular prices a week before. Most embassies were seen confronting the hotels. When they found nothing satisfactory, they sent complains to the Ministry.
Worried by the number of complaints, MoFA called on the hotels and Ministry of Culture and Tourism (MoCT) on many occasions to at least consider and not to overstate the rate of changes in the prices. However, the increase in the charges of many hotels was found to be more than fourfold. A USD 100 costing room service now goes for $400 to 500.
Few months back, Mihretab Mulugeta, director of protocol at MoFA, warned that the exaggerated increases of prices need to be taken care of before it is too late. During a meeting held with hotel owners at that time, he recalled that many hotels were found increasing prices fourfold. Even Sheraton Addis was spotted for double increase in prices during AU’s summit last year, Mihretab said.
Sisay Teklu, director of the stakeholder’s relation directorate at the MoCT also fears that if the hiking price continues to be the trend here, Ethiopia will lose its biggest shares of the international tourism conference business. The worst is that many international conferences no longer will come to the country. However, he said that only a few hotels have increased prices and some handful of them end up below the expected number of customers.
According to Sisay, a ten or twenty percent increment may not harm anybody in the business but it will negatively implicate if the prices are not considerate of the country’s image. Furthermore, the services provided are the other alarming areas in which the ministry says working on to address it promptly.
Source: http://www.ezega.com
Ethiopia, Brazil Sign Cooperation Agrements
May 27, 2013 - In Brazil’s first ever presidential visit to Ethiopia on Friday, May 24, the two countries signed four cooperation agreements that Ethiopian officials consider signal the entry of the emerging South American powerhouse into a large scale involvement in Ethiopia’s economy, according to Capital.
The two sides signed cooperation agreements in areas of agriculture, aviation science and technology as well as education. Brazil’s Foreign Minister, Antonio Patriota, signed the first three agreements with Ethiopia’s Agriculture Minister, Tefera Deribew, Transport and Communication Minister, Diriba Kuma, and Science and Technology Minister, Mahamuda Gass.
The agreements were signed in Addis Ababa after Brazil’s President, Dilma Vana Rousseff, and Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn held talks on bilateral cooperation at the Prime Minister’s Office.
The Latin American emerging power has growing interests in Africa particularly in the areas of mining while African countries are showing growing interests for investments and financial deals with Brazil.
Accordingly, there has been growing diplomatic relations between the two sides over the last 10 years. During this decade, for example, Brazil opened 17 embassies in Africa raising its diplomatic missions in the continent to 37, according to a Brazilian Foreign Ministry official who came with the presidential delegate. Its embassy in Addis Ababa is on the list of the re-opened.
Rousseff has, therefore, come to Addis Ababa with a number of senior officials including her Foreign Minister, Antonio Patriota, Education Minister as well as directors of Petrobras and Brazil’s Development Bank.
According to the Foreign Ministry official, the two leaders have discussed on future cooperation in the areas of mining and investment financing.
Rousseff is in Addis Ababa to attend the Special Summit of the African Union that took place yesterday in celebration of the 50th anniversary of the Pan-African organization. On Saturday morning she took part in a high level debate of African leaders at the AU headquarters. She also spoke at the special summit held at the Millennium Hall of Addis Ababa.
Source: http://www.ezega.com
Monday, May 27, 2013
Brazil Development Bank Gives $1 Billion to Ethiopia Rail
Ethiopia will receive $1 billion in funding from the Brazilian Development Bank to build a section of a railway that will be extended to connect to neighboring South Sudan, a Foreign Ministry official said.
Andrade Gutierrez Participacoes SA of Brazil will build the link running from the capital, Addis Ababa, to Jimma about 439 kilometers (273 miles) to the southwest, Taye Atskeselassie, director general for the Americas at the ministry, said in an interview on May 24.
The bank “is willing to finance the project,” he said after Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn met Brazilian President Dilma Rousseff. “The technical side has been finalized, it’s only the financing part; it’s a matter of the details.” Construction will begin “soon,” he said.
Ethiopia, Africa’s second-most populous nation, needs funding to build 4,744 kilometers of electrified railway lines at a cost of 110.8 billion birr ($5.9 billion) as it seeks to develop a cheaper alternative to moving goods by road. Economic growth may slow to 6.5 percent this year and next, compared with average growth of 8.7 percent over the past five years, according to the International Monetary Fund.
Export-Import Bank of China signed a loan agreement worth nearly $3 billion for a railway from Addis Ababa to the port of Doraleh in neighboring Djibouti, the state-owned Ethiopian Radio and Television Agency reported last week.
The government of Turkey is funding a separate route, while Ethiopia is negotiating with Russia and India to finance and build other rail projects, Ethiopian Railways Corp. said on April 26.
Officials from Petroleo Brasileiro SA, Brazil’s state-run oil company, attended last week’s meeting, Taye said. “They are very much interested in doing business as well here, but no specific issues have been raised at this time,” he said.
Hailemariam and Rousseff signed cooperation agreements on air transport, science and technology, education and agriculture, Ethiopia’s State Minister of Foreign Affairs Berhane Gebrekristos said.
“This is a turning point in Ethiopian-Brazilian relations,” Berhane said.
To contact the reporter on this story: William Davison in Addis Ababa at wdavison3@bloomberg.net
To contact the editor responsible for this story: Antony Sguazzin at asguazzin@bloomberg.net
Source: http://ethioprofessionals.com
Thursday, May 23, 2013
የመብራት ያለህ…
አሁን አሁን የመብራትና የስራ እንዲሁም የመብራትና የሰው ቁርኝት በጣም የሚገርም ነው፡፡ ያለመብራት መስራት ድሮ ቀረ እኮ፡፡ ምክንያቱም ሁሉ ነገር በኮምፒዩተር ነው የሚሰራው፡፡ በተለይማ በመስሪያ ቤቶች አካባቢ የሚስተዋለው መብራት ሲጠፋ የሆነ ብርሃን ያለበት አካባቢ የቢሮው ሰራተኛ ይሰበሰብና መዓት ወሬ ይቸረችራል፡፡ በቤት ጉዳይ፣ በመብራት ጉዳይ፣ ስለሀገሪቷ ተጨባጭ ሁኔታ፣ ስለ ምሳ፣ ወ.ዘ.ተ… ብቻ ምን አለፋችሁ World Atlas ውስጥ የሌለ ነገር ሁሉ ይሰማል፡፡ እናም ምን ልላችሁ ነው፤ የሰው ልጅ ከህያውነቱ ወደ ሮቦትነት ተቀይሯል፤ መብራት ሲጠፋ ልክ እንደ ሮቦት ቀጥ፡፡ ምንም ያክል በእጅ የሚሰራ ስራ ቢኖር እንኳን መብራት ከጠፋ የስራ ሙድ አብሮ ይጠፋል፡፡
This shows the ultimate dependency syndrome of electricity (power). In this world we live in right now, nothing can be done without power and computer. Because it is the time of Artificial Intelligence than natural intelligence.
መብራት ኃይል ደግሞ የሆነ የቁማር ጨዋታ ይጫወት ይመስል ይህን ሁሉ ነገር እያወቀ ጢባ ጢቤ ይጫወታል፡፡ የሚገርመው እኮ የመብራት ኃይል መስሪያ ቤት ራሱ መብራት ከጠፋ ስራ ማቆሙ ነው፡፡ ይህ ሁሉ ተጠራቅሞ የሀገሪቷን ኢኮኖሚ እንደሚያሽመደምደው ሳይታለም የተፈታ፤ ፀሃይ የሞቀው እውነታ ነው፡፡ ባለጉዳይ ይጉላላል፤ ፋብሪካዎች ይቆማሉ፤ የተጀመረ ስራ እንደተጀመረበት ሰዓት ምርታማ ሆነህ መብራት ከመጣ በኋላ መቀጠል አትችልም፡፡
ስለሆነም በእነ ጊቤ፣ ተከዜ፣ አዋሽ፣ እና አባይ አምላክ መብራት ኃይል ወደፊቱን ቢያስተካክል ጥሩ ነው፡፡ “አንድ ጎልና አንድ ባል አያስማምንም” እንደሚባለው መብራት ኃይል እና ቴሌ አንድ ለሀገሪቷ ስለሆኑ አማራጭ መጠቀም አልተቻለም፡፡ ስለዚህም ነው እንደፈለጉ የሚጫወቱብን፡፡ ለማንኛውም ይህ ከላይ የጠቀስኩት ሁሉ እሮሮ መስተካከል አለበት ለማለት ያህል ነው፡፡
Tuesday, May 21, 2013
አይ ቤት….
“ቤት” ማለት የሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎቶች ከሚባሉት ከምግብና ከልብስ በኋላ የሚመጣው ነው፡፡ ወይም አነስ ባለ ቃል “መጠለያ”፡፡ ታዲያ የሰው ልጅ ሆኖ ተፈጥሮ እነዚህ ፍላጎቶች ሳይሟሉለት መኖር ምን ይባላል፡፡ በእርግጥ እንኳን እንደ ኢትዮጵያ ባለች ድሃ አገር በጣም በለፀገች በምትባለው፣ ሰማይን በአንድ አይናቸው የሚጠቅሱ ፎቆች ባሉባት አገር (ከፔንታጎን መንትያ ህንፃዎች ጀምሮ፤ አሁን በህይወት ባይኖሩም)፣ ከዓለም የበላይ ነኝ በምትለው፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፅ/ቤት የሚገኝባት፣ ልዕለ-ኃያል ነኝ በምትለው፣ ሥመ-ጥር ባለፀጋዎች ያሉባት አሜሪካን እንኳን ቤትና መጠለያ የሌላቸው ብዙዎች ናቸው፡፡ ግን በእኛ ሀገር ላይ በጣም ይብሳል፡፡ ቤት የሌለውን ከመቁጠር እኮ እውነቴን ነው የምላችሁ ያለውን መቁጠር ይቀላል፡፡ ምክንያቱስ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በግምት ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው ህዝብ የሚኖረው በኪራይ ነው እኔ እንደሚገባኝ፡፡ ለዛውም አከራዮች እንደ ሎሌ ሆነው እንደልባቸው እየፈነጩበት፡፡ ከቀሪዎቹ 40 በመቶዎች ደግሞ ቢያንስ 35 በመቶው እንደ ቤት በማይቆጠሩ የተቀዳደደ የድሃ ብርድ ልብስ የሚመስል ጣሪያ ባላቸው፤ ውሃ በነፃ የሚያስገቡ ማለቴ ነው፤ በእነዚህ ቤቶች ውስጥ ነው የሚኖሩት፡፡ ስለዚህ ደልቶት የሚኖረው ህዝብ ከ5 በመቶ በላይ ይሆናል ብዬ አላስብም፡፡ ታዲያ ይህ ሆኖ እያለ ቤት (ኮንዶሚኒየም) እየሰሩ መስጠት ለምን ዘግይቶ ተጀመረ? በእርግጥ የተፈናቀሉ ሰዎችን በእጅጉ እየጠቀመ ነው፡፡ ነገር ግን በ1997 ዓ.ም. ከተመዘገቡት ውስጥ እስካሁን የደረሳቸው ግማሽ እንኳን አልደረሱም፡፡ ለምንድን ነው መሰራቱ ካቀረ በብዛት ተሰርቶ በቤት እጦት ለሚሰቃዩ ነዋሪዎች የማይበረከተው፡፡ ዞሮ ዞሮ ገንዘብ ይከፍሉበታል፡፡ እናም እኔ የምለው የሚሰሩት ቤቶች ጥራታቸውን ጠብቀው፣ ዘመን የሚሻገሩ ሆነው ቢሰሩ ምንድን ነው ኃጢያቱ? ይቅርታ አድርጉልኝና እዚህ አገር የሚሰሩ ስራዎች ጠቅላላ ሲሰሩ ከ20 ዓመት በላይ ወደፊት የማይሻገሩ ስራዎች ናቸው የሚሰሩት፡፡ የወደፊቱ ትውልድ ታሳቢ ተደርጎ ቢሰራ እኮ ለጊዜው ነው ትንሽ ወጪ የሚጠይቀው እንጅ ለሀገሪቷ መፃኢ ህይወት በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ በሌሎች ያደጉት ሀገራት እኮ በ18ኛው ክፍለ ዘመን የተሰሩ ህንፃዎች ናቸው ከመኖሪያነት ጀምሮ እስከ ቤተ-መንግስትነት የሚጠቀሙት፡፡ ለዚህም ነው ለግንባታ የሚወጣውን ወጪ ለሌሎች የልማት ስራዎች እያዋሉ ሊመነደጉ የቻሉት፡፡ አሁንም እኮ ከአሁን በፊት 3000 ዘመን እንዳደረግነው ልንቀጥል ነው፡፡
ስለሆነም እኔ የምለው የሚሰሩት ቤቶች ጥሩ አቅምና እድሜ እንዲኖራቸው ተደርገው ቢሰሩ ጥሩ ነው፤ የማንም አሸዋና ሲሚንቶ በትክክል ቀላቅሎ በማይሰራ ተለማማጅ ኢንጂነር ነኝ ባዮች መለማመጃ ሆኖ እንዳይቀር፡፡ ልክ በቅርቡ እንደተስተዋለው በጀሞ ኮንዶሚኒየም ሰዎች ውስጥ እያሉ እንዳዘመመው ቤት፡፡ በዚህ ከተቀጠለ መጨረሻው አያምርም፡፡
Thursday, May 16, 2013
የከፍተኛ መንግስት ባለስልጣናት የሀብት ምዝገባ
የኢትዮጵያ ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከሁለት ዓመት በፊት ገደማ ጀምሮ እንደ አጀንዳ ይዞ በተለያዩ ሚዲያዎች ሲወራ ሰምተናል፣ አይተናል፣ አንብበናል፡፡ ኮሚሽኑ በተደጋጋሚ ቆጠራና ምዝገባ ከተጠናቀቀ በኋላ ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን ቃል ገብቶ ነበር፡፡ ይሁንና ይኸው ከሁለት ዓመት በላይ በኋላም ምንም ጠብ ያለ ነገር የለም፡፡ የተሰማ ነገር የለም፡፡ 2005ም ሊያልቅ ነው፤ መስከረም ሊጠባ ነው፡፡ ሲጀመር እኛ ተቆጥሮ ይነገረን አላልንም፤ ከተባለ በኋላ ግን አፋችንን ከፍተን ስንጠብቅ ነበር፡፡ ነው ወይስ ተቆጥሮ አላልቅ አለ፤ የተበታተነ ንብረት ካለ ምናልባት፡፡ ባለስልጣኖቻችን እንደሆኑ እንግዲህ በPay roll ነው የሚከፈላቸው፡፡ እንበልና አንድ ባለስልጣን ከ83 ዓ.ም ጀምሮ ስልጣን ላይ ቢሆንና እስከ 2005 ዓ.ም በየወሩ 4,000 የኢትዮጵያ ብር የተጣራ ደሞዝ ቢከፈለው ሂሳቡ፡-
4,000ብር X 22ዓመት X 12ወራት = 1,056,000 ብር ይሆናል፡፡
ይህን የሚያጠራቅመው ደሞዙን ለምንም ነገር ባያውለው ማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ባለስልጣኖቻችን መቼም ማክያቶ ለመጠጣት ጊዜ የላቸውማ፡፡ ለነገሩማ እንደሚወራው ከሆነ እኮ የሚከፈላቸው ደሞዝ አነስተኛ ቢሆንም፤ ብዙ ጠያቂ አላቸው ነው የሚባለው፤ ልክ ሰሞኑን እንደተስተዋለው የጉምሩክ ባለስልጣና ኃላፊዎች በተግባር እንዳሳዩት ማለት ነው፡፡ ልክ በጃንሆይ ጊዜ ሲደረግ እንደነበረው ማለት ነው፡፡ አንድ ጉዳይ ለማስፈፀም በግ እየጎተቱ የሚሄዱበት ጊዜ ነበር፤ አሁን አድጎ በውጭ ምንዛሬ፣ በህንፃዎች፣ በፋብሪካዎች፣ ወ.ዘ.ተ… ሆኗል፤ ምክንያቱስ ከአገራችን እድገት አንፃር ነዋ፡፡ በነገራችን ላይ ሙስና ባይኖር እኮ አዲስ አበባችን እነዚህን በመሳሰሉ ረዣዥም ህንፃዎች አትሽቆጠቆጥም ነበር፤ ጠቀሜታውን ከዚህ አንፃር እንቃኘው፡፡
ወደ ዋናው ጉዳይ ልመልሳችሁና ይህች ተቆጥራ የምታልቅ የPay roll ገንዘብ እንዴት የህን ያህል ጊዜ እንደፈጀች ሊገባኝ አልቻለም፡፡ ቢሆንም በቀጣዩ ምርጫም ጊዜ ቢሆን እኛ እንዲነገረን እንፈልጋለን፡፡ በደሞዙ እየተሸማቀቀ፣ የቤት ኪራይ ከደሞዝ በላይ የሚከፍል፣ የሚበላው፣ የሚጎርሰው፣ የሚለብሰው፣ የሚጠጣው ያጣ የመንግስት ሰራተኛ (Civil Servant) ተብሎ ግብዳ ስም ወጥቶለት የሚኖር ስንቱ ነው መሰላችሁ፤ ብቻ “ቤት ይቁጠረው” ወይም “ሆድ ይፍጀው” ብለን እንለፈው እንጂ፡፡ “ሁሉን ሲናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል” ነው ያለችው ዘፋኟ፡፡ “Civil Servant” የሚለው ቃል “የህዝብ አገልጋይ” የሚል አቻ ትርጓሜ ያለው ሲሆን፤ የሚሰጠው ደሞዝና ክብር ግን በድሮ ጊዜ “ባሪያ” ተብለው እየተገረፉ ሲሰሩ ከነበሩት በጣም የወረደ ነው፤ ለዛውም የዛን ጊዜ ባሪያዎች የሚበሉት እስከሚጠግቡ ነው፤ ለሚኖሩበት ቤት አይጨነቁም፡፡ እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው የህዝብ አገልጋዩ ተሰቃይቶ እንዲኖር የተፈረደበት ይመስል፤ እንዲሁ ቀን ያልፋል እያለ እየተንፏቀቀ እየኖረ ይገኛል፡፡ ይህ ሁሉ እሮሮ የሁሉም የመንግስት ሰራተኛ ነው፡፡ ኑሮ ሲወደድ፣ የእቃ ዋጋ ሲንር፣ የሚጠቀመው ነጋዴውና የግል ተቀጣሪው ነው፡፡ እነሰሱ አያግኙ ማለቴ አይደለም፡፡ ነጋዴዎች የገበያ ላይ ዋጋ ሲጨምሩ ለመንግስት ሰራተኛው ትንሽ ድጎማ ቢጤ ታስፈልጋለች ማለቴ ነው፡፡ ዋናውን ርዕሴን ትቼ ወደ እሮሮ ገባሁ እኮ፤ ይቅርታ ይህ ነገር ስለሚከነክነኝ ነው፡፡ ብዙ ጓደኞቼ የመንግስት ሰራተኛ በመሆናቸው የማየውን ነው ያወራሁት፡፡ ስለሆነም በመጨረሻ የባለስልጣኖቻችን ሀብት ተቆጥሮ፣ ሰባራ ሳንቲም ሳይቀር፣ እንዲነገረን እንፈልጋለን፡፡
Ethiopian Overlooked and Underutilized Sector - Agriculture
Agriculture is the prominent sector of Ethiopia which millions of lives depend on for centuries. The share still stands high compared ...

-
የ11ኛው ዙር አጠቃላይ የአዲስ አበባ 20_80 ኮንዶሚኒየም ቤት ፕሮግራም አሸናፊዎች ዝርዝር ለማየት ቀጣዩን ሊንክ ይጫኑ https://drive.google.com/file/d/0B7AnIIjHSJxNVEpqc1V4NXVtMz...
-
ጅቦች መብታችን ማስከበር አለብን በማለት ፍርድ ቤት ቀርበው ክስ መሰረቱ። ጅቦቹም “ቆይ እኛ በዚህች አገር ስንኖር መድሎ ለምን ይፈጸምብናል? ከአንበሳ እኩል እየታየን አይደለም!” በማለት አቤቱታቸውን ለዳኛው ያቀርባሉ፡፡ ...
-
ይህ የምታዩት ምስል የምሁሮች መፍለቂያ ከሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ዋናው በር አጠገብ ያነሳሁት ነው፡፡ በትልቁ “ማንኛውንም ማስታወቂያ መለጠፍ ክልክል ነው” የሚል ማስታወቂያ ቢለጠፍም ብዙ ማስታወቂ...